Get Mystery Box with random crypto!

እድሜ መሄዱ ካልቀረ! አንድ የ30 አመት ጎልማሳ ብዙ ከወላወለ በኋላ እድሜ ልኩን ሲመኘው የነበረ | Our World

እድሜ መሄዱ ካልቀረ!

አንድ የ30 አመት ጎልማሳ ብዙ ከወላወለ በኋላ እድሜ ልኩን ሲመኘው የነበረን የምህንድስና ትምህርት ለመማር ለምዝገባ ወደ አንድ ኮሌጅ ሄደ፡፡ ቢሮ እንደገባ የተማሪዎች አማካሪ አገኘውና ሲያማክረው፣ “በመማርና ባለመማር መካከል ብዙ ወላውያለው” አለው፡፡

አማካሪው ምክንያቱን ሲጠይቀው፣ “አሁን 30 አመቴ ነው፡፡ ስመረቅ እኮ 35 ሊሆነኝ ነው” በማለት የመወላወሉን መነሻ ምክንያት ነገረው፡፡
አማካሪው የመለሰለት መልስ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ትምህርት ገፋው፡፡ “የዛሬ አምስት አመት እኮ ብትማርም ሆነ ባትማር 35 አመት መሙላትህ አይቀርም፡፡ ሳትማር 35 አመት ከሚሞላህ፣ ተምረህ ቢሞላህ አይሻልም?”

እስቲ አንድ ጊዜ ጸጥ በሉና ስንት እድሜ ላይ እናዳላችሁ አስቡት፡፡ ከዚያም በአሁኑ እድሜያች ላይ አምስት አመት ደምሩበት፡፡ ድምሩ ስንት መጣ?

በሉ እንግዲህ . . .

• ብትማሩም ሆነ ባትማሩም የዛሬ አምስት አመት እድሜያችሁ በአምስት አመት መጨመሩ አይቀርም! ሳትማሩ ከሚጨምር፣ እየተማራችሁ ቢጨምር አይሻልም?

• ብትነግዱም ሆነ ባትነግዱም የዛሬ አምስት አመት እድሜያችሁ በአምስት አመት መጨመሩ አይቀርም! ሳትነግዱ ከሚጨምር፣ እየነገዳችሁ ቢጨምር አይሻልም?

• ብታቅዱም ሆነ ባታቅዱም የዛሬ አምስት አመት እድሜያችሁ በአምስት አመት መጨመሩ አይቀርም! ሳተቅዱ ከሚጨምር፣ አቅዳችሁና ተንቀሳቅሳችሁ ቢጨምር አይሻልም?

በእድሜ ምክንያት ከመንቀሳቀስ ራስን ማገድ ማለት፣ ነገ መሞቴ ካልቀረ ዛሬውኑ መኖርን ላቁምና እንደሞተ ሰው ልኑር እንደማለት ነው፡፡
በሉ ተንቀሳቀሱ !!!

መልካም ቀን!