2022-07-01 13:59:21
ተጎጂዎችን ጎብኝተዋል
=================
ከውጭና ከውስጥ ጠላቶች ጋር በመተባበር ሃገር ለማፍረስ እየሠራ እንደሆነ በሚጠቁም መልኩ ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ መግለጫ የተሰጠበት የአሕባሽ ቡድን፤ በትናንትናው ዕለት የአዲስ አበባ መጅሊስን አጥር ሰብሮ በንብረትና በሰው ላይ ቀላል የማይባል ጉዳት ማድረሱ ይታወሳል።
በዕለቱ የከተማ አስተዳደሩ በአንድነት ፓርክ ባዘጋጀው መሰናዶ ላይ ተጋብዘው የተገኙት የአዲስ አበባ መጅሊስ ፕሬዝዳንት "ሐጂ" ሱልጧን አማን ኤባና በወንበደዎቹ ለሰዓታት ታግተው የነበሩት ጸሐፊያቸው ሸይኽ ሐሚድ ሙሳ፤ በዛሬው ዕለት ትናንት ከፍተኛ ድብደባ የተፈጸመበትን መቶ አለቃ ዓሊን በቤቱ በመገኘት ጎብኝተዋል።
ወንድማችን ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን የደበደቡት አረመኔዎች ሙቷል ብለው በሊፍት መውጫው ጉድጓድ ውስጥ ሊጥሉት እንደነበር፤ ከዚያም ከመካከላቸው አንዱ «በሶፋ ወንበር ሸፍኑት!» ብሎ ጮኾ ወንበሩን እንደጫኑበት መናገሩ ተሰምቷል።
ለዚህ አረመናዊ ድርጊት መንግስት እርምጃውን እንዲወስድ እንጠይቃለን። ይበቃል
አሕባሽ ከዚህም በላይ ሃገር ሳያፈርስ በጊዜ መላ ሊበጅለት ይገባል።
379 viewsAhmad hamadi, 10:59