እንዴት ቢነገረን ነው የሚገባን? ማንስ ቢነግረን ነው የምንሰማው? ልባችንም እንዴት ነው የደነደነው? እስከመቼ ነው በዝማሬያችን እንደዘፈን የምንዘለው? ማንስ ነው ያስተማረን? በዝማሬ የምትዘሉ ተመስጦን እንደ ምክንያት የምታነሱ ክህነት ያላችሁ፣ መዘምራን እና ሁላችሁም ምዕመናን በሙሉ እንኳን ልትመሰጡ ይቅርና ተመስጦ ውስት ያለውን እራሱ ከተመስጦ ታወጣላችሁ። ከውበትም አንጻር ከሆነም በጣም ያስጠላል። "ነገር ግን ሁሉ በአገባብና በሥርዓት ይሁን።" 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 14:40 13.4K viewsedited 14:20