Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክሳዊ ግጥሞች 📜

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodox_poem — ኦርቶዶክሳዊ ግጥሞች 📜
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodox_poem — ኦርቶዶክሳዊ ግጥሞች 📜
የሰርጥ አድራሻ: @orthodox_poem
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.91K
የሰርጥ መግለጫ

💠
እንኳን ደና መጡ!
በቻናላችን ላይ ኦርቶዶክሳዊ
ጥቅሶች እና ግጥሞችን 📜 ያገኛሉ።
💠
@Eotc_books
@Orthodox_film
@Orthodox_poem
@Orthodox_bealat
@Orthodox_question
@Orthodox_mezemur
@Orthodox_Tewahdo_picture
💠
@EOTC_LIBRARY
@EOTC_LIBRARY_BOT
💠
ለአስተያየት ➱ @Orthodox2_bot
💠

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-05-13 22:14:27 አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ

አባ አባ ብዬ በለመንኩህ ለቅሶ ተሰምቷል ጩሀቴ
በውን ያስጨነቀኝ ተራራው ፈተና ተነስቷል ከፊቴ
የተማመንኩበት የሥምህ ስንቅነት አንዳች አልጎደለ
ተስፋ ያደረግሁት የጸሎትህ ሥምረት በሕይወቴ አለ

የተደገፍኩበት የደጅህ ዋስ’ነት ሜዳ አልጣለኝም
እንባ የረጨሁበት የ’ስማኝ!’ ዋይታዬ አልወደቀብኝም
ከህጻንነቴ አንተን ተማምኜ የሄድኩበት መንገድ
በጥቅጥቁ ጫካ አንበሳው አልነካኝ አልሆንኩ አልቦ ዘመድ

ልጅነቴ ሁሌ ገብረ ሕይወት እያለች በምልጃህ ተማምና
ትናንት እንዳልተውካት ዛሬም ስትጣራህ ለነፍሴ ጭንቅ ና፡፡
አቡየ አቡየ ብዬ ሀገር አሻግሬ ስምህን እጠራለሁ
ከግብጽ በረሃ ለምትሻህ ኢትዮጵያ ቶሎ ና እላለሁ

ታስፈልጋታለህ እንኳንና ለሰው ለአናብስት ሁሉ
የጽድቅህን ፍሬ የቀመሱ ነፍሳት አባ አባ ይላሉ
የንጽኅናህ ግርማ ከግብጽ እስከ ኢትዮጵያ ሀገር እያወደ
አንበሳውም ነብሩም እያገለገለህ አንተን እያጀበ ካንተ ጋራ ሄደ

አቡዬ ና ድረስ ና ገስግስ ዘንድሮም ቶሎ ና ለሀገሬ
እረፉ በላቸው እንዳይናከሱ ሰውንና አውሬ
ዛሬም ቁም ዝቋላ ግባ ከባህሩ እጆችህን ዘርጋ
ፈልግ ልጆችህን የጸሎት ፍሬህን የጠበቅኸውን መንጋ

ከሰሜን ከደቡብ ከምስራቅ ከምዕራብ የተጋደልህለት
“ኢትዮጵያን ማርልኝ !” ብለህ ከአምላክህ ፊት ብዙ የጸለይክለት
የረገጥከው መሬት ያረፍክበት ደብር የነካህ አፈሩ
ዳግም በዛሬው ቀን ጸሎትህን ይሻል መላው ሀገሩ

ምድረ ከብድ ድረስ ተገኝ በዝቋላ አንሳ እጆችህን
እስከምንጠገን ተሰብረናልና እየን ልጆችህን
አታሳፍረንም ገብረ መንፈስ ቅዱስ ብለን ስንጠራህ
እንግዲህ አቡኤ የኢትዮጵያን ነገር አሁንም አደራህ

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ግጥሞች እና
ጥቅሶች ቻናል

{{ @orthodox_poem }}

@EOTC_library
@EOTC_library_bot
https://t.me/+YZYAOpgOgns2Njdk
13.5K viewsedited  19:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-04 08:13:47 ++ ሥነጽሑፍ - ግጥም !

( ርዕስ - ምን አሉ ? )

ምን ነበር ያሉት አበው ሲናገሩ
የታሪክ አደራ የቅርሳቸው ክብሩ
ለምን ነበር ይጨነቁ የነበሩ
ስለምን ነበር ያስቡ የነበሩ
ስጋቸውን ለማስደሰት
ያመረና የጣመ ለመብላት
በእስፕሪንግ አልጋ ላይ ለመተኛት
ቢሮ ተቀምጦ ዳቦ ለመብላት
ባለስልጣን ሆነው ለመታየት
ስለምን ነበር ሲያስቡ የነበሩት
ስለምን ነበር ሲናገሩ የነበሩት
ምን ተብሎ ተጽፎ ስለ እነርሡ ክብር
ምን ተብሎ ታወሰ የእነርሡ ዝክር
ብርሀናው ይውጣ ይነገር ሥራቸው
ዳግም ይነገር ይታይ ውጤታቸው
ብርሀናው ከወጣ ከተፈለገ ሥራቸው
አስታዋሽ ካገኛ ከታየ ሥራቸው
እንዲህ ነበር አበው የታሪክ ገድላቸው
ገና ጉዞውን ሲጀምር የክርስትናውን
ከሰባት ወንድሞች ጋር በአበው የተሾመው
ያ ታለቅ አባት የወንጌል አርበኛው
በአንድ ስብከት 12ሺህ ያተመቀው
ምን አለ እስጢፋኖስ በድንጋይ ሲወግሩት
ስጋውን ቆራርጠው ደሙን ሲያፈሱት
እንደ ስንዴ ክምር ድንገይ ሲጭኑበት
ስለምን ተናገረ ምና ብሎ መሰከረ
ጌታ ኢየሱስ ሆይ ነፍስን ተቀበል
ጌታ ሆይ ይህን ኃጢያት አትቁጠርባቸው
ያ አረጋዊ ታላቅ አባት
ጌታን የሚወደው ከሁሉ በፊት
ሲናገር ቀደም ቀደም ብሎ የሚመሠክረው
ከጌታ ስብከት ለአፍታ ያልተለየው
አንተ ከምትሞት እኔ ልሙት ያለው
የመንግስተ ሰማያት ቁልፍ አደራ የተሰጠው
በጎቹን እንዲያሰማራ ቃል የገባው
ለመሆኑ ምን አለ ጴጥሮስ ያ ታላቁ አባት
ጌታ ሆይ ወዴት ትሄዳለህ ደግመኛ
በሮም አደባበባይ ልሰቀል ሲለው
ጌታ ሆይ አንተ ከምትሰቀል እኔ እሰቀላለሁ
ስለመንግስተ ሠማያት ሲከራከሩ ሀዋሪያት
ጌታችን በምሳሌ የነበረው አቅርቦት
ያ ታናሽ ብላቴና ያልተለየው ከዮሐንስ
የሠማውን ለማስተላለፍ የተሯሯጠው በእግር በፈረስ
ምን አለ አግናጢዎስ ለባሴ እግዚአብሔር ምጥው ለአንበሳ
በትርኢት ቀርቦ በሮም አደባባይ ሲሰዋ
ዛሬ ተረኛ ነኝ በአምላክ እንደንጹህ መገበሪያ ስንዴ ልቀርብ ይገባኛል አለ
በ451 በጉባኤ ኬልቄዶን
እንዲቀበል ተገደደ ሁለት ባህሪይን
በበክርሊያና መለቂያ በሀይል የታዘዘው
ወልድ ዋህድ አንድ ባህርይ ብሎ የመሰከረው
የበርክሊያንና የመርቂልያን ዱላ የጠገበው
በግዞት የተሰደደው
ጥርሱ በግፍ የወለቀው
ፅህሙ በግፍ የተነጨው
ምን አለ ዲዮስቆሮስ ያ ታላቅ ባለሙያ
ምን ብሎ መሰከረ ስለምንስ ተናገረ
ጥርሱንና ጽህሙን በመሀረብ አስሮ ክርስቲያኖች
ይህ የሀይማኖት ፍሬ ነው በርቱ አይዟችሁ
ምን አለች ያቺ ታላቅ እናት
በስጋ ስትኖር ዓለምን የናቀች
ምን ያደርግልኛል ብላ በልጅነቷ የመነነች
የሰውን ልጅ ከአምላክ ለማስታረቅ የበቃች
ደግሞም ሰይጣንን ለማስታረቅ የለመነች
የዓለምን አምልኮት ታግላ ያሸነፈች
ለስጋዋ ሳይሆን ለነፍሷ የቆመች
ለብልጭልጭና ለጌጥ እጇን ያልሰጠች
በአጓጉል ፋሽን ያልተንበረከከች
በስጋዊ ምኞት በሀይሏ የገደለች
ለመሆኑ ምን አለች ክርስቶስ ሰምራ
ዘብሄረ ቡልጋ የኢትዮጲያ የቅርስ አደራ
ሳጥናኤል ሆይ ሳጥናኤል ሆይ ና ውጣ
ከአምላክህ ጋር ላስታርቅህ ማነው
በክብር ስሜ የጠራኝ ብሎ ሲናገር ሚካኤል ደርሶ በሰይፍ መታው
ይህ ነበረ የአበው ገድላቸው
የቅድስና ስራ የክብር ጌጣቸው
ይሄን ነበር ያሉት አበው በቃላቸው
ለትውልድ እንዲተላለፍ የፃፉት በደማቸው
ስጋቸውን ቆርሰው አጥንታቸውን የሰበሰቡት
ህይወታቸውን ለክርስቶስ እንደስንዴ መገበሪያ የሰጡት
ኸረ ዛሬስ ምን አለን እኛ
የአበው ልጆች የተቀበልን አደራ
በእነርሱ እግር ለመተካት የጀመርን ስራ
ምን ነበር ስራችን ጌጥ ክብራችን
ስለምን ነበር ሀሳብ ጭንቀታችን
የእኛ ጭንቀትማ እንደው ከተነሳ
ስጋን ለማስደሰት የምናየው አበሳ
ድንቅና ውብ አድርጎ በፈጠረው አካላችን
ይበልጥ ለማሳመር ስናደርግ አዲስ ፋሽን
ግድግዳ ይመስል ቀለም ስንቀባው
የጠቆረውን ለማቅላት ብራውን እያልን ስንከልሰው
በዓለም ፋሽን ይበልጥ ስናጌጠው
እንደልኳንዳ ቤት ስጋ በመቶ ሻማ ስናሳየው
ይሄ ነው ጭንቀታችን ሀሳብ ክብራችን
ለመሆኑ ምን አላችሁ መናፍቅ ቤታችሁ ሲገባ
ወንጌል ተሰበኩ ብሎ ሊላችሁ አላስወጣ አላስገባ
ምን ብላችሁ መለሳችሁ ስለምንስ አወራችሁ
ጀርመናዊ በንዴ ወንጌልን ለመስበክ ሲመጣ
ከተማራችሁት ውጭ አዲስ ቃል ሲያመጣ
ምን ብላችሁ መለሳችሁት ይህን መናፍቅ
ዘመቻ ተብሎ በአንድ ቃል ሲታወጅባችሁ
መዳን አለባችሁ ተብሎ ሲሰብክላችሁ
ቃሉን አልሰማችሁም ስሙ ስትባሉ
ለመሆኑ ምን አላችሁ
ከአበው አባቶች የተቀበልነውን አደራ
እንድንወጣ አምላክ ይሁን ከእኛ ጋራ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር ይቆየን !


የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ግጥሞች እና
ጥቅሶች ቻናል

{{ @orthodox_poem }}

@EOTC_library
@EOTC_library_bot
12.2K views05:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-01 08:17:52


ወደ ቻናላችን በመቀላቀል

➲ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መፅሐፍትን በPDF
➲ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ጥያቄዎችን
➲ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙራትን በ audio
➲ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ፊልሞችን
➲ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ግጥሞች እና ጥቅሶችን
➲ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክብረ በዓላትን ያግኙ


@EOTC_library
@EOTC_library_bot

https://t.me/+YZYAOpgOgns2Njdk
https://t.me/+YZYAOpgOgns2Njdk





♡ ㅤ ❍ㅤ ⎙ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ᵘⁿᵐᵘᵗᵉ ᶜʰᵃⁿⁿᵉˡ
5.7K views05:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-29 18:36:46
#ቤተክርስቲያንን_አትንኩብን
#ወራቤ_ላሉ_ክርስቲያኖች_ድምፅ_ነኝ
5.4K views15:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-28 21:11:05 https://t.me/+YZYAOpgOgns2Njdk
6.7K views18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-27 14:24:44            #በዘንባባሽ_ባርኪኝ


  #በዘንባባሽ_ባርኪኝ አርሴማ
#የተጋድሎሽ_ዜና በአለም ተሰማ
በረከትሽ ብዙ ቃልኪዳንሽ ሀያል
ስምሽን ጠርቼ ልቤ መች ይረካል
 #በጨለማዉ_ልሂድ ቢበዛ መከራ
ሁሉን አለፈዋለዉ #ስምሽን_ስጠራ
              
ገድልሽን ስሰማ ደነቃት ሂወቴ
#ዘንባባሽን_ይዘሽ ግቢልኝ ከቤቴ
   ፀሎቴ ደረሰ ስለቴ ተሰማ
ሞገሴ ሆነሻል #እናቴ_አርሴማ
             
  አጋንት ወደቁ ሲጠራ ስምሽ
#ልዩ_ክብር_አለሽ አምላክ የሰጠሽ
 #ነይ_ተመላለሺ ግቢ ከቤታችን
 #የሂወትን_ፅዋ ይዘሽ ለነብሳችን

 
የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ግጥሞች እና
ጥቅሶች ቻናል

{{ @orthodox_poem }}

@EOTC_library
@EOTC_library_bot
9.1K views11:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ