2022-06-29 16:45:30
. በድጋሜ ታላቅ የምስራች
ለ ኦሜጋ ት/ቤት ወላጆች/አሳዳጊዎች
ሰራተኞች እና ማህበረሠብ በሙሉ
እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን
ኦሜጋ ትምህርት ቤት በ18/10/2014ዓ/ም በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ በተደረገ የእውቅናና ሽልማት መርሃ ግብር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ዳሬክተር ዶ/ር እሸቱ ለማ ፣የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል ረዲ ፣የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አለማየው ፍቃዱ፣ የፅዳት አምባሳደር ሻምበል አርቲስት ስዩም ዘለቀ ፣የከተማ የክ/ከተማ የወረዳ አመራሮች ፣የየት/ቤቱ አመራሮች መምህራን ተማሪዎች ፣የሃይማኖት አባቶች እና የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች በተገኙበት በኮልፌ ቀራንዮ ካሉት የመንግስት እና የግል ትምህርት ቤቶች መካከል በተደረገ በ2014 በጀት ዓመት በተካሄደ 3ኛው ዙር ከተማ አቀፍ የፅዳት ንቅናቄ ዘመቻ ፣ እና ቆሻሻን መልሶ በመጠቀም ውድድር ኦሜጋ ትምህርት ቤት አንደኛ ( 1ኛ) ደረጃ በመውጣቱ ከኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል ረዲ የዋንጫ እና የምስክር ወረቀት ተበርክቶልናል::
1.4K views13:45