2022-07-01 18:14:01
. ታላቅ የምስራች
ለ ኦሜጋ ት/ቤት ወላጆች/አሳዳጊዎች
ሰራተኞች እና ማህበረሠብ በሙሉ
እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን
ኦሜጋ ትምህርት ቤት በ22/10/2014 ዓ/ም በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 በተደረገ የእውቅናና ሽልማት መርሃ ግብር የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ፀሀይ አስማረ ፣ የወረዳው የትምህርት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙሉጌታ ሽብሩ ፣የት/ቤቱ አመራሮች መምህራን ተማሪዎች ፣የሃይማኖት አባቶች፣የወረዳው የፅዳት አምባሳደሮች እና የወረዳው ነዋሪዎች በተገኙበት ከኮልፌ ቀራንዮ ወረዳ 09 ከሚገኙ በርካታ የመንግስት እና የግል ትምህርት ቤቶች መካከል በ2014 በጀት ዓመት በተካሄደ 3ኛው ዙር ከተማ አቀፍ የፅዳት ንቅናቄ ዘመቻ እና ቆሻሻን መልሶ በመጠቀም ውድድር ኦሜጋ ትምህርት ቤት አንደኛ ( 1ኛ) ደረጃ በመውጣቱ ከኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ፀሀይ አስማረ እጅ የዋንጫ እና የምስክር ወረቀት ተበርክቶልናል::
1.3K views15:14