Get Mystery Box with random crypto!

የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ የክረምት የሕዋ ሥልጠና መርሃግብር በጅማ ዩኒቨርሲቲ ዛሬ መሠጠት | Ethiopian Space Science Society

የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ የክረምት የሕዋ ሥልጠና መርሃግብር በጅማ ዩኒቨርሲቲ ዛሬ መሠጠት ተጀመረ።

በመረሃግብሩ ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ዋናው መሥሪያቤት የመጡ አሰልጣኞች፣ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ጅማ ቅርንጫፍ አመራሮች ፤ የጅማ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ተወካዮች ፣ እንዲሁም ሌሎች የዩኒቨርሲቲው ማሕበረሰብ አባላት ተገኝተዋል።

ሠልጣኞቹ በጅማ ከተማ የተውጣጡ ተማሪዎች ሲሆኑ ከነኅሴ 23 እስከ 27 በሚቆየው በዚህ የክረምት የሕዋ ስልጠና መሠረታዊ የሆኑ የሥነ-ፈለክ፣ የሳተላይት ቴክኖሎጂ እንዲሁም የኤሮስፔስ ምህንድስና ዘርፎች ተግባራዊ የሆኑ ሥልጠናዎችን ይወስዳሉ።

የኢት.ስ.ሳ.ሶ የክረምት ሥልጠና በዚህ ክረምት ከሚያካሂዳቸው 5 የሥልጠና መረሃግብሮች ይህ የመጨረሻው እና የመዝጊያ ሥልጠና ነው።


#ESSS #SST #Jimma