እስራኤል የኢትዮጵያ መንግሥት የዴር ሡልጣን ገዳም ይዞታን እንዲያስጠብቅ አሳሰበች ንሥር ብሮድካስት ሰኔ 28/2015 በግብፅ ኮፕቲክና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መካከል አለመግባባት የሚፈጥረው የዴር ሡልጣን ገዳም ይዞታ፤ የኢትዮጵያ ሆኖ እንዲዘልቅ እንደሚፈልግ የእስራኤል መንግሥት ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ኢየሩሳሌም የሚገኘውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ንብረት የሆነውን የዴር ሡልጣን ገዳም ይዞታ ማስጠበቅ አለበት ሲሉ፤ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አለልኝ አድማሱ ተናግረዋል፡፡ የእስራኤል መንግሥት የዴር ሡልጣን ገዳም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይዞታ ነው ብሎ እንደሚያምንም አምባሳደሩ ገልጸዋል ሲል አዲስ ማለዳ ዘግቧል፡፡ ወቅታዊ ፤ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት Youtube: https://www.youtube.com/@nisir/videos FaceBook Page 1 : https://www.facebook.com/Nisirbroadcast FaceBook Page 2: https://www.facebook.com/Nisirmereja Telegram: https://t.me/nisirbroadcasting Website: https://nisirbroadcasting.com Twitter: https://twitter.com/NISIRInternati1 Instagram: https://www.instagram.com/nisirbroadcast/ ንሥር ብሮድካስትን በወዳጅነት ይከታተሉን። 594 views09:26