Get Mystery Box with random crypto!

ለአዲስ አበባ ሙስሊም ማህበረሰብና ለመስጂድ ጀመዓዎቸ ከአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር | NidaTube -ኒዳ ቲዩብ

ለአዲስ አበባ ሙስሊም ማህበረሰብና ለመስጂድ ጀመዓዎቸ ከአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የተላለፈ ጥሪ

ነገ እሁድ መጋቢት 3 | 2015 ከጠዋቱ 12:30 ሰዐት ጀምሮ ጉለሌ በሚገኘው የሙስሊሞች መካነ መቃብር ቅጥር ግቢ የማይቀርበት ቀጠሮ ተይዟል።

ቀጠሮው ወጣት ወንዶችን ይመለከታል።

ስራው ወደ ጫካነት ተለውጦ የጅቦች መራቢያ፣ የሌቦች መደበቂያ፣ የሱሰኞች መነሀሪያ የሆነውን ጉለሌ መካነ መቃብርን ጫካውን በመመንጠር ምቹ የቀብር ስፍራ ማድረግ ነው።

በዚህ ትልቅ አጅር በሚያስገኘው በጉልበታችን ብቻ በሚሰራው ኸይር ስራ ላይ ወላጆች እና ሴቶች ወንድ ልጆቻችሁን እና ወንድሞቻችሁን በመላክ እና በማበረታታት የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ።

ይህ ስፍራ የነገው የእያንዳንዳችን ማረፊያ ነው ቤታችንን እናፅዳ ቤታችንን ምቹ እናድርግ።

ነገ በፍፁም አይቀርም ጠዋት 12:30 ሰዐት ላይ እንገናኝ።

የጉለሌ ሙስሊም መካነ መቃብር አድራሻውን ለማታውቁ

ከፒያሳና አካባቢው ለምትመጡ:-

እንቁላል ፋብሪካ አደባባዩን አልፋችሁ ወደ ጎጃም በረንዳ በሚወስደው መንገድ በስተ ግራ በኩል

ከአለም ባንክ፣ ጦርሀይሎችና አካባበከው ለምትመጡ:- ከአውቶብስተራ ወደ ፓስተር ስትሄዱ በስተቀኝ በኩል ሁለተኛ አስፓልት ቂያስ ወደ ሀግቤስ በሚወስደው መንገድ ላይ ወደ ግራ በሚወስደው በመታጠፍ በስተቀኝ በኩል ቀብሩን ታገኙታላችሁ

ከአስኮ እና አከባቢ ለምትመጡ:- ከፓስተር አደባባይ እንዳለፋችሁ ኖክ ማዲያ ፊት በስተቀኝ በኩል ወደ ጨው በረንዳ ስትታጠፉ ቀብሩን በግራ በኩል ታገኙታላችሁ

ከጥቁር አንበሳ ለምትመጡ ደግሞ አንዋር መስጂድን አልፋችሁ በቀኝ በኩል ወደ አዲሱ ገበያ የሚወስደውን አስፓልት አልፋችሁ ወለጋ ሆቴል በሚገኝበት አስፓልት ወደቀኝ በመግባት ውሀ ልማቱ ፊት ታገኙታላችሁ
@nidatube