በትግራይ ክልል መደበኛ ትምህርት ሚያዝያ 23/2015 ዓ.ም ይጀመራል።
በትግራይ ክልል ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል መደበኛ ትምህርት ሚያዝያ 23/2015 ዓ.ም እንደሚጀመር የጊዜያዊ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።
የጊዜያዊ መንግስት በተቋቋመባቸው የክልሉ አካባቢዎች መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደቱ እንደሚጀመር የቢሮው ኃላፊ ኪሮስ ጉኡሽ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
"በክልሉ ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ 2.4 ሚሊዮን ተማሪዎችን ወደ ትምህርታቸው ለመመለስ ምዝገባ እንደሚደረግ" ኃላፊው ገልጸዋል።
@News_for_student
@News_for_student