Get Mystery Box with random crypto!

‹‹ልጆቻችንን በማለዳ ማን እንደወሰደብን አናውቅም፡፡ እባካችሁ ልጆቻችንን አፋልጉን፡፡›› ወላጆች | Nedir Nun || ነዲር ኑን 😍

‹‹ልጆቻችንን በማለዳ ማን እንደወሰደብን አናውቅም፡፡ እባካችሁ ልጆቻችንን አፋልጉን፡፡›› ወላጆች
(Please SHARE! Spread it.)
**********
በፎቶው ላይ የምታዩዋቸው ሁለት ሕጻናት አስማ ናስር እና ሐሰን ናስር ይባላሉ፡፡ ወንድምና እህት ናቸው፡፡ አስማ ዕድሜዋ 13 ሲኾን፣ ሐሰን የ10 ዓመት ሕጻን ነው፡፡ ሳዑዲ አረቢያ የተወለዱት እነዚህ ሕጻናት፣ ከወላጆቻቸው ጋር በቅርቡ ነው ወደ ኢትዮጵያ ተባረው የመጡት፡፡ በደንብ መናገር የሚችሉት ቋንቋም አረብኛ ነው፡፡

ትናንት ሐሙስ ማለዳ 11፡00 ገደማ አሸዋ ሜዳ፣ አብድ ኖኖ ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ ጀርባ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው፣ ወላጅ አባታቸው አቶ ናስር ለሱብሒ ሶላት ወደ መስጊድ ሲወጣ በመኝታ ክፍላቸው ነበሩ፡፡ ነገር ግን አቶ ናስር ከሶላት ሲመለስ ሁለቱን ሕጻናት ልጆቹን ና ለጊዜው ፎቶዋ ያልተገኘ አብራቸው የምታድግ ፈትሂያ ኑራ የተባለች የ11 ዓመት ሕጻን በቤቱ ውስጥ አጥቷቸዋል፡፡

እናታቸው ተኝታ ስለነበር፣ ልጆቹ ወዴት እንደሄዱ፣ ምን እንዳገኛቸው፣ ማን እንደወሰዳቸው ያወቀችው ነገር የለም፡፡

እናም፣ "እባካችሁ ወገኖቻችን፣ ልጆቻችንን አፋልጉን" ሲሉ በፈጣሪ ስም ተማጽነዋል፡፡

የአባታቸው ስልክ ቁጥር 0960-04 37 67 ነው።
***
እባካችሁ ይህን መልዕክት ሼር በማድረግ ሦስቱ ሕጻናት እንዲገኙ እንተባበር፡፡