Get Mystery Box with random crypto!

አንድት ሴት ከመገላለጥ ትጠንቀቅ አንቺ ውዷ እህቴ ሆይ ዛሬ ላይ ብዙሃ | የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

አንድት ሴት ከመገላለጥ
ትጠንቀቅ



አንቺ ውዷ እህቴ ሆይ ዛሬ ላይ ብዙሃን ሴቶች እያደረጉት ያለው ድርጊት ከትልልቅና አፀያፊ ወንጀል ተደርጎ ይወሰዳል፦ ከቤታቸው ሌሎችን አማላይና ለራሳቸው የማለሉ ሆነው ተቀባብተው ተውበው መውጣታቸው ትልቅ የፊትና በር ከፋቾች ሆነዋል።

ያም ጌጥን ውበትን መገላለጥ
ሸቶ መቀባባት የተላያዩ ፈታኝ የሰውነት ክፍሎችን ማሳየት ወንዶችን መቀላቀል ይህ አስቀያሚ ድርጊት ይፈፅማሉ በራሳቸውም ላይ የአሏህን ቁጣ ያረጋግጣሉ።


قال الله تعالى: - (وَمَا ظَلَمْنَاهُمْ وَلَٰكِن ظَلَمُوا أَنفُسَهُمْ ٍۖ )
هود (101)

አሏህ እንድህ አለ፦ 【እኛ አልበደልናቸውም ነገር ግን እነሱ እራሳቸውን በደሉ።】
ሱረቱል ሁድ [101]

والله عز وجل يقول : " وَقَرْنَ فِي بُيُوتِكُنَّ وَلَا تَبَرَّجْنَ تَبَرُّجَ الْجَاهِلِيَّةِ الْأُولَى " [سورة الأحزاب، الآية : 33].

አሏህ እንድህ አለ፦ ((ቤታችሁ ተቀመጡ የቀደምት የመሀይማንን አገላለጥ አትገላለጡ))።
ሱረቱል አህዛብ [33]

ويقول سبحانه : " وَلَا يُبْدِينَ زِينَتَهُنَّ " [سورة النور، الآية : 24].

ሉኡሉ ጌታችን ይላል፦ ((ጌጣቸውን ግልፅ አያድርጉ))
ሱረቱ ኑር [24]

وقال النبي صلى الله عليه وسلم «صنفان من أهل النار لم أرهما : قوم معهم سياط كأذناب البقر يضربون بها الناس، ونساء كاسيات عاريات مائلات مميلات رءوسهن كأسنمة البخت المائلة، لا يدخلن الجنة ولا يجدن ريحها، وإن ريحها ليوجد من مسيرة كذا وكذا»
رواه مسلم وغيره

የአሏህ ነብይ እንድህ አሉ፦ «ሁለት አይነት ሰዎች የእሳት ናቸው አሁን አላያቸውም ፤ ሰዎች ናቸው ከነሱ ጋር ሰዎችን የሚደበድቡበት የከብት ጅራት መሰል አለንጋ ያላቸው ፣ እናም ለብሰው ያለበሱ ለራሳቸው የሚማልሉ ሌሎችንም የሚያማልሉ ሴቶች ናቸው ፀጉራቸው እንደተዘነበለ ግመል ሻኛ ነው ጀነት አይገቡም ሽታዋንም አያገኙም…።»
ሙስሊምና ሌሎችም ዘግበውታል

አንድት ሙስሊም የሆነች ሴት ጠባብ ዘርዛራ የሰውነት ቅርፅን ከሚያሳይ የሰውነትን ውበት ከሚያጋልጥ ልብስ መራቅ ይኖርባታል።

እንድሁም ከመሰባበር ድምፅን ከማቅለስለስና በአካሄድ ሰዎችን ከመፈተን ልትጠነቀቅ ይገባታል።

ከራሷ ላይ ሂጃብ ማንሳት ከደረት ከክንድ ከባት መሰል የሰውነት ክፍሎችን መግለጥን ትጠንቀቅ።
ጋጠ ወጥ የሆኑ ሴቶች የሚለብሱትን አይነት አጫጭር ልብስ ከመልበስ ልትጠነቀቅ ይገባታል።
ይህ አሏህ እርም ክልክል ካደረገው ነገር ስለሆነና እንድሁም ለአደገኛ ፊትና ስለሚያጋልጥ።

قال العلامة ابن باز رحمه الله :
فالواجب الحذر من ذلك، والمرأة عورة وخطرها عظيم على نفسها وعلى غيرها، فالواجب عليها أن تكون بعيدة عن أسباب الفتنة بالتحجب ولبس الجلباب الذي يسترها ...

ኢማም ኢብኑ ባዝ አሏህ ይዘንላቸው እንድህ ነበር ያሉት፦
«ግዴታው ከዚህ ልትጠነቀቅ ነው ፣ ሴት ሰውነቷ በሙሉ ሃፍረተ ገላ ነው ፣ አደጋዋም በራሷም ሆነ በሌሎች ላይ የከፋ ነው ፣ ግደታው እሷነቷን ልሸፍን የሚችለውን ጅልባብ በመልበስ ከፊትና ምክናየቶች የራቀች ልትሆን ነው…።»

ሴት ሰውነቷ በሙሉ ሊገለጥ የማይገባው ሃፍረተ ገላ ነው ወደ ሱቅ ስትወጣ ሸይጧን ይክባታል።
ለዚህም ልትሸፈንና ሂጃቧን አጥብቃ ልትይዝ ይገባታል ይህ የሰላም ምክናየት ስለሆነ።

والله يقول سبحانه في كتابه العظيم: (وَإِذَا سَأَلْتُمُوهُنَّ مَتَاعًا فَاسْأَلُوهُنَّ مِنْ وَرَاءِ حِجَابٍ ذَلِكُمْ أَطْهَرُ لِقُلُوبِكُمْ وَقُلُوبِهِنَّ )[الأحزاب:53]،

አሏህ በተከበረው ቃሉ እንድህ አለ፦ 【እቃን ስትጠይቁ ከመጋረጃ ጀርባ ሆናችሁ ጠይቁ ይህም ለናንተም ሆነ ለነሱ ልብ ንፅህና የተሻለ ነው።】
ሱረቱል አህዛብ [53]

እህቴ በመሸፈንሽ የሌሎችንም የራስሽንም ልብ ከተለያዩ በሽታዎች ትጠብቂያለሽ።

እህቴ አሏህ ይዘንልሽ እነዚያ ምርጥ ቆነጃጅት የነብዩ ምርጥ የነብዩ ባልደረቦች የነበሩት ጀግና ሴቶችን ሞደል አድርጊ ፤ እነዚህ ዛሬ ላይ ክብራቸውን ማንነታቸውን አርግፈው የጣሉ ክብራቸው መደፈሩ የማያሳስባቸው የዝንብ መዋያ የሆኑ ሴቶች እስታይል እንዳይሸውድሽ ስልጣኔ መስሎች የስልጣነውን ማማ የስልጣነውን ሰገነት አውልቀሽ አልሰለጠነው አውሬነት እንዳትመለሽ።

ያነበባቹህ በሙሉ ሼር

የሴት ልጅ መስተካከከል
ለኢስላም ኡማ ቁልፍ ነዉ

ለሂዳያ ስበብ አንሁን
ለወድ እህቶቼ አድርሱልን

SHARE SHARE
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ