Get Mystery Box with random crypto!

'የዕለት አንጀራችንን ዛሬ ስጠን' . ለምን የዕለት እንጀራ ኾነ? በሌላ አባባል ለምን የዕለ | ናዝራዊ Tube

"የዕለት አንጀራችንን ዛሬ ስጠን"



.
ለምን የዕለት እንጀራ ኾነ? በሌላ አባባል ለምን የዕለት ብቻ? ለዕድሜ ዘመናችንን የሚበቃውን ኹሉ አንዴ ቢዘረግፍልን ምናለበት? ወይም ለምን የ10 ዓመት ዕቅዳችንን የሚሸፍን እንጀራ አንጠይቅም? የ50 ዓመቱን ብንለምነውስ? የሰማኒያውንስ ቢኾን? እርሱ እንደ ኾነ ኹሉ የተረፈው ነው፤ ምን አለበት የዳቦ ተራራ ቢሰጠን?

የዕለት እንጀራችንን እንዲሰጠን እግዚአብሔርን መለመን ያለብን ለምንድን ነው? እኛ የሕይወታችን ባለቤት አይደለንም። የህልውናችን ምንጭ እግዚአብሔር ስለ ኾነ ራሳችንን አላስገኘንም። ሕይወት የእግዚአብሔር ስጦታ ናት፤ የግል ርስታችን አይደለችም። “የሕያዋን ኹሉ ነፍስ፥ የሰውም ኹሉ መንፈስ በእጁ ናት[ና]” (ኢዮ 12፥10)፥ ለመገኘታችን ሌላ ሰበብ አልነበረም፤ የለምም። ከእርሱና በእርሱ ተገኝተናል፤ ወደ እርሱም እንመለሳለን። በፍጥረትም ኾነ በድኅነት የተቀበልነው ሕይወት ምንጭ ሕያው አምላክ ነው።

ሕይወታችን የምታሣሣ ችግኝ ነች። እግዚአብሔር ራሱ ከሕይወት ውሃ ካላጠጣን ለዘላለሙ ደርቀናል። እርሱ ጥላ ከለላ ካልኾነልን ላለመለምለም ጠውልገናል። እርሱ ካላቆመን ላለመነሣት ወድቀናል። እርሱ ካልሰበሰበን ለዘላለሙ ተበትነናል። …

የዘላለም ሕይወት የሰጠን አምላክ ምድራዊ እንጀራም ይሰጠናል። በሰብአዊ ኀይል፥ በቍሳቍስና በምድራዊ ባለጠግነት ሕይወታችንን አናጸናውም። ዕውቀትና ጥበባችን አልፈጠረንምና ገንዘባችን ሕይወት አልሰጠንምና የራሳችን አይደለንም። የሕይወታችን ባለቤት የፈጠረን አምላክ ነው። የሕይወታችን ባለቤትና ጌታ እግዚአብሔር ራሱ ነው። ያስብልናል። …

እግዚአብሔር የሕይወታችን ባለቤት ብቻም ሳይኾን መጋቢና ጠባቂዋ ነው። አንጡራ ሀብታችን፥ ገንዘባችንና ቍሳቍሳችን አሳዳሪዎቻችን አይደሉም። በዘላለም ሕይወት ዋስትናም አያኖሩንም። ዋስትናችን መግቦቱ ነው።

እውነተኛ አማኝነት በእግዚአብሔር ላይ የተደገፈ ሕይወት ነው። ከገበታችን ላይ በቀረበልን የዕለት ምግባችን ጀርባ የተወሳሰበ ምጋቤ ሀብታዊ የምግብ ሰንሰለት አለ። ከመጨነቅ ይልቅ በእግዚአብሔር ላይ ያለ ቋሚ መታመን ዋስትና ያስገኝልናል። ዲትሪክ ቦኖፈር “ክርስትያን መጨነቅ እንደማይችል እና እንደማይደፍር ብቻ ሳይኾን መጨነቅ እንደማያስፈልገውም ያውቃል። የዕለት እንጀራውን የሚያገኘው በመጨነቁ ወይም በመሥራቱ አይደለም፤ ምክንያቱም እንጀራ የአባት ስጦታ ነውና።” …
.
ሙሉውን ለማግኘት፦



ሰሎሞን አበበ ገብረ መድኅን (መጋቢ)