ጳውሎስ ፈቃዱ “እነዚህ ወንጌላዊ ክርስቲያኖችን አይወክሉም፤ ከእኛም ጋር በሃይማኖት አንድ አይደሉም። እነርሱ ነን ስላሉ ብቻ የእኛ አካል አድርገን አንወስዳቸውም። በሃይማኖት አንድ አይደለንም፤ እኛንም ሊወክሉን አይችሉም” ሲሉ ጠንከር ያለ ትችታቸውን ይሰነዝራሉ። የወንጌላዊ አብያተ ክርስትያናት ኅብረት ፕሬዝዳንት የሆኑት መጋቢ ጻድቁ አብዶም፣ በመጋቢ ጳውሎስ ሀሳብ ይስማማሉ። የሥነ መለኮት መምህሩ ተካልኝ ነጋ (ዶ/ር ) በበኩላቸው በምዕራቡ ዓለም እነዚህ ሰዎች የሚጠሩበት ስያሜ ፓስቶፕረነር (pastopreneur ) እንደሚባል በመጥቀስ “ነጋዴዎች” ይሏቸዋል። https://www.bbc.com/amharic/articles/czq0xq7zzv9o 309 viewsΒενιαμίν, 18:56