ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ለፀጥታ አካላት በተዘጋጀው የእውቅና መርሃ ግብር ለመታደም አሶሳ ገቡ። #Ethiopia : የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ሰላምና ፀጥታን ለማስከበር ለሠሩ የፀጥታ አካላት በተዘጋጀው የእውቅና መርሃ ግብር ለመታደም አሶሳ ከተማ ገብተዋል፡፡ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ወደ ከተማዋ ሲገቡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰንን ጨምሮ የካቢኔ አባላት አቀባበል ማድረጋቸውን ኤፍቢሲ ዘግቧል። በመርሃ ግብሩ ለመከላከያ ሰራዊትና ለሌሎች የፀጥታ ኀይሎችና ተቋማት እውቅና እንደሚሰጥ ይጠበቃል። 28.6K views11:22