"ሪያል ማድሪድን በተከታታይ ጊዜ ማሸነፍ ቀላል አይደለም"
ስፔናዊዉ የውሀ ሰማያዊዎቹ አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ከሪያል ማድሪድ ጋር ከሚያደርጉት ጨዋታ በፊት በጋዜጣው መግለጫ ንግግር አድርጓል።
"ጨዋታውን ለመቆጣጠር ብቻ አይደለም ወደዚህ ምንመጣው ፣ ሪያል ማድሪድን ለመጉዳት ፣ እነሱን ለመቅጣት፣ ጎል ለማግባት መሞከር አለብን። "
"የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አንዴ ብቻ ማንሳት ለማን ሲቲ በቂ አይደለም"
"ሪያል ማድሪድን በተከታታይ ሁለት ጊዜ በተመሳሳይ መንገድ ማሸነፍ ግን ቀላል አይደለም..."
"ማድረግ ያለብን ነገር ላይ እናተኩራለን ፣ የተቀናቃኞቻችንን የጥንካሬ ነጥቦችን እንፈትሻለን እና ለእሱ እንዘጋጃለን። ግን በእግር ኳስ ጨዋታ ላይ እናተኩራለን"ሲል ጋርዲዮላ ተናግሯል።
ፔፕ ጋርዲዮላ አክሎም ስለ ጁድ ቤሊንግሃም እንዲህ ብሏል፦ "ልዩነቱን የሚያደርገው በጭንቅላቱ ውስጥ ያለው ነገር ነው ፤ እሱ አስደናቂ የውድድር ዘመን እያሳለፈ ነው ፤ በጣም ወጣት ነው ፤ ወደፊትም አስደናቂ የእግርኳስ ህይወት ይጠብቀዋል"ሲል ተናግሯል።
SHARE @MULESPORT