Get Mystery Box with random crypto!

የትምህርት ሚኒስቴር

የቴሌግራም ቻናል አርማ ministery_of_education — የትምህርት ሚኒስቴር
የቴሌግራም ቻናል አርማ ministery_of_education — የትምህርት ሚኒስቴር
የሰርጥ አድራሻ: @ministery_of_education
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 29.03K
የሰርጥ መግለጫ

ትምህርት ሚኒስትር @MINISTERY_OF_EDUCATION

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2018-12-31 18:49:20 በተማሪዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በአማራና በኦሮሞ ተማሪዎች መካከል #ግጭት እንዲነሳ ያስተባበሩ ተማሪዎችን ለ1 አመት ከትምህርት እንዲታገዱ መወሰኑን አስታወቀ፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ እንዳስታወቀው በዩንቨርሲቲው ውስጥ ከሁለት ሳምንት በፊት በተማሪዎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት ግጭት ተከስቶ ሁለት ቀናት የመማር ማስተማር ሂደቱ መቋረጡን ገልጸው የሌሎችን አላማ ለማሳካት ተልእኮ ወስደው በአማራና ኦሮሞ ተማሪዎች መካከል ግጭት እንዲነሳ ያደረጉ 10 ተማሪዎች ለአንድ አመት ከትምህርት እንዲታገዱ መወሰኑን ገልጸዋል፡፡

በዩኒቨርሲቲው ግጭት በተከሰተበት ወቅት የሃይማኖት አባቶችና የሃገር ሽማግሌዎች ጨምሮ በአካባቢውና በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ እርቀ ሰላም ለመፍጠር በተደረጉ ተከታታይ ውይይቶች ለብጥብጡ መነሳት ጉልህ ድርሻ የነበራቸው ተማሪዎች ተለይተው ተመጣጣኝ እና አስተማሪ እርምጃ ይወሰድባቸው በሚል የአካባቢው ነዋሪዎችና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ያነሱትን ተደጋጋሚ ሀሳብ መነሻ በማድረግ መሆኑን ገልጿል፡፡

ይህንን መሰረት በማድረግ በዩንቨርስቲው በነበረው ግጭት አነሳሽ እና ባለቤት በመሆን ግጭቱን በመምራት ያስተባበሩ ተማሪዎችን በዩኒቨርሲቲው ህግ መሰረት ኮሚቴ በማዋቀርና በማጣራት 24 ተማሪዎችን በመለየት 10ሩ ለአንድ አመት ከትምህርት እንዲታገዱ፣ 5ቱ ከባድ የፁሑፍ ማስጠንቀቂያ፣ 9ተማሪዎች ደግሞ የመጨረሻ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸው ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ በዩንቨርስቲው ሴኔት ውሳኔ አስተላልፏል።

አንድ አመት የተቀጡት ተማሪዎች ያጠፉት ጥፋት በዩኒቨርሲቲው ህግ መሰረት እድሜ ልክ ከትምህርት የሚያሰናብትና በማስጠንቀቂያ የታለፉትም ከሁለት ዓመት ያላነሰ ቅጣት የሚያስቀጣ ቢሆንም የሚከተሉት የቅጣት ማቅለያ ምክንያቶችን፦

1. ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታው ገፊ ምክንያት ስለሆነ
2. ተማሪዎች ወጣቶች በመሆናቸው ሌሎች ኃይሎች በቀላሉ ሊገፋፏቸው የሚችሉበት ሁኔታ ከፍተኛ ስለሆነ
3. ዩኒቨርሲቲው እርምጃውን ሲወስድ ዓላማው ማስተማር ብቻ ስለሆነ
4. ተፈጥሮ የነበረውን ግጭት በማብረዱና የነበረውን ሁኔታ በመመለሱ ረገድ ተማሪዎች ራሳቸው ከፍተኛ ድርሻ የነበራቸው በመሆኑና ሌሎችን ጉዳዮች ታሳቢ በማድረግ እንደሆነ ገልጾ የተቀጡ ተማሪዎች ቅጣታቸውን ጨርሰው ሲመለሱ መልካም ስነ ምግባር ያላቸው መሆኑን የሚገልጽ ማስረጃ ከሚኖሩበት ቀበሌ ማምጣት እንደሚጠበቅባቸው ዩኒቨርሲቲው አስታውቋል፡፡

በሌላ በኩል በዩኒቨርሲቲው አጥፊ የሆኑ ተማሪዎች በጥፋታቸው መሰረት ባሉበት ዩኒቨርሲቲ ተገቢውን እርምት እንዲወስዱ ማድረግና ከሚኖሩበት ማህበረሰብ ጋር ተመሳስለው እና ተቻችለው እንዲኖሩ ማስተማር ሲገባ ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ እንዲዛወሩ ማድረግ መርህ አልባ አሰራር ከመሆኑ ባሻገር ለዩኒቨርሲቲውም ሆነ ለሀገሪቱ መፍትሄ ነው ብሎ ዩኒቨርሲቲው እንደማያምን ገልጿል፡፡

ይሁን እንጅ ሰሞኑን ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ከሌላ ቦታ የዝውውር ደብዳቤ ለአንድ ተማሪ ተጽፎለት አልቀበለው አለ በሚል አንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች መነሻ ምክንያቱን ሳይረዱ የሚሰጡት ትችት አዘል አስተያየት ትክክል ነው ብሎ አያምንም ብሏል፡፡

ለእያንዳንዱ ችግር በስሜት የምንወስደው የመፍትሄ አማራጭ በዩኒቨርሲቲዎች ያለውን የሰላማዊ መማር-ማስተማር እጦት ይበልጥ እያወሳሰበውና በሀገሪቱ የታየውን ተስፋ ለማጨለም ሌት ተቀን ለሚሰሩ አካላት ተጨማሪ ኃይል እንዳንሆናቸው ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግና ሁሉን ነገር በሰከነ መንገድ የማየት ልምድ ማዳበር አለብን ብሏል የሆነው ሆኖ ዩኒቨርሲቲው ተማሪውን ተቀብሎ ያስተናገደው መሆኑን መግለጽ እንወዳለን፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

ትምህርት ሚኒስቴር
@MINISTERY_OF_EDUCATION
94.7K viewsHENOK, 15:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2018-12-31 18:47:34 ትምህርት ሚኒስቴር:
በተማሪዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በአማራና በኦሮሞ ተማሪዎች መካከል #ግጭት እንዲነሳ ያስተባበሩ ተማሪዎችን ለ1 አመት ከትምህርት እንዲታገዱ መወሰኑን አስታወቀ፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ እንዳስታወቀው በዩንቨርሲቲው ውስጥ ከሁለት ሳምንት በፊት በተማሪዎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት ግጭት ተከስቶ ሁለት ቀናት የመማር ማስተማር ሂደቱ መቋረጡን ገልጸው የሌሎችን አላማ ለማሳካት ተልእኮ ወስደው በአማራና ኦሮሞ ተማሪዎች መካከል ግጭት እንዲነሳ ያደረጉ 10 ተማሪዎች ለአንድ አመት ከትምህርት እንዲታገዱ መወሰኑን ገልጸዋል፡፡

በዩኒቨርሲቲው ግጭት በተከሰተበት ወቅት የሃይማኖት አባቶችና የሃገር ሽማግሌዎች ጨምሮ በአካባቢውና በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ እርቀ ሰላም ለመፍጠር በተደረጉ ተከታታይ ውይይቶች ለብጥብጡ መነሳት ጉልህ ድርሻ የነበራቸው ተማሪዎች ተለይተው ተመጣጣኝ እና አስተማሪ እርምጃ ይወሰድባቸው በሚል የአካባቢው ነዋሪዎችና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ያነሱትን ተደጋጋሚ ሀሳብ መነሻ በማድረግ መሆኑን ገልጿል፡፡

ይህንን መሰረት በማድረግ በዩንቨርስቲው በነበረው ግጭት አነሳሽ እና ባለቤት በመሆን ግጭቱን በመምራት ያስተባበሩ ተማሪዎችን በዩኒቨርሲቲው ህግ መሰረት ኮሚቴ በማዋቀርና በማጣራት 24 ተማሪዎችን በመለየት 10ሩ ለአንድ አመት ከትምህርት እንዲታገዱ፣ 5ቱ ከባድ የፁሑፍ ማስጠንቀቂያ፣ 9ተማሪዎች ደግሞ የመጨረሻ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸው ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ በዩንቨርስቲው ሴኔት ውሳኔ አስተላልፏል።

አንድ አመት የተቀጡት ተማሪዎች ያጠፉት ጥፋት በዩኒቨርሲቲው ህግ መሰረት እድሜ ልክ ከትምህርት የሚያሰናብትና በማስጠንቀቂያ የታለፉትም ከሁለት ዓመት ያላነሰ ቅጣት የሚያስቀጣ ቢሆንም የሚከተሉት የቅጣት ማቅለያ ምክንያቶችን፦

1. ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታው ገፊ ምክንያት ስለሆነ
2. ተማሪዎች ወጣቶች በመሆናቸው ሌሎች ኃይሎች በቀላሉ ሊገፋፏቸው የሚችሉበት ሁኔታ ከፍተኛ ስለሆነ
3. ዩኒቨርሲቲው እርምጃውን ሲወስድ ዓላማው ማስተማር ብቻ ስለሆነ
4. ተፈጥሮ የነበረውን ግጭት በማብረዱና የነበረውን ሁኔታ በመመለሱ ረገድ ተማሪዎች ራሳቸው ከፍተኛ ድርሻ የነበራቸው በመሆኑና ሌሎችን ጉዳዮች ታሳቢ በማድረግ እንደሆነ ገልጾ የተቀጡ ተማሪዎች ቅጣታቸውን ጨርሰው ሲመለሱ መልካም ስነ ምግባር ያላቸው መሆኑን የሚገልጽ ማስረጃ ከሚኖሩበት ቀበሌ ማምጣት እንደሚጠበቅባቸው ዩኒቨርሲቲው አስታውቋል፡፡

በሌላ በኩል በዩኒቨርሲቲው አጥፊ የሆኑ ተማሪዎች በጥፋታቸው መሰረት ባሉበት ዩኒቨርሲቲ ተገቢውን እርምት እንዲወስዱ ማድረግና ከሚኖሩበት ማህበረሰብ ጋር ተመሳስለው እና ተቻችለው እንዲኖሩ ማስተማር ሲገባ ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ እንዲዛወሩ ማድረግ መርህ አልባ አሰራር ከመሆኑ ባሻገር ለዩኒቨርሲቲውም ሆነ ለሀገሪቱ መፍትሄ ነው ብሎ ዩኒቨርሲቲው እንደማያምን ገልጿል፡፡

ይሁን እንጅ ሰሞኑን ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ከሌላ ቦታ የዝውውር ደብዳቤ ለአንድ ተማሪ ተጽፎለት አልቀበለው አለ በሚል አንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች መነሻ ምክንያቱን ሳይረዱ የሚሰጡት ትችት አዘል አስተያየት ትክክል ነው ብሎ አያምንም ብሏል፡፡

ለእያንዳንዱ ችግር በስሜት የምንወስደው የመፍትሄ አማራጭ በዩኒቨርሲቲዎች ያለውን የሰላማዊ መማር-ማስተማር እጦት ይበልጥ እያወሳሰበውና በሀገሪቱ የታየውን ተስፋ ለማጨለም ሌት ተቀን ለሚሰሩ አካላት ተጨማሪ ኃይል እንዳንሆናቸው ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግና ሁሉን ነገር በሰከነ መንገድ የማየት ልምድ ማዳበር አለብን ብሏል የሆነው ሆኖ ዩኒቨርሲቲው ተማሪውን ተቀብሎ ያስተናገደው መሆኑን መግለጽ እንወዳለን፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

ትምህርት ሚኒስቴር
@MINISTERY_OF_EDUCATION
85.4K viewsHENOK, 15:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2018-12-30 21:07:54 ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ማሳሰቢያ

በተለይ #ለፍሬሾ ተማሪዎች

ጉዳዩ የዩኒቨርስቲውን ህግ እና ደንብ ስለ ለማስታወስ

ዩኒቨርስቲ ከሌሎች የትምህርት ተቋማት የተለየ እና ጠንከር ያለ ህግ እና ስርዓት ያለው እንደሆነ ይታወቃል።ነገር ግን አንዳንድ ተማሪዎች ባለማወቅም ሊሆን ይችላል፡ ይህንን ደንብ እና ስርዓት እየተላለፋችሁ ነው።

ከነዚህም አንዱ አለአግባብ እየጮኻችሁና ሴቶችም ላይ ከባድ ተፅዕኖ እየፈጠራችሁ እንደሆነ አስተውለናል።
በተለይ አካባቢው ባለበት ሁኔታ ውስጥ አላስፈላጊ #ጩኸት ሌላ ትርጉም ስላለው ትልቅ አደጋ አለው።
***
ሌላው በተለይ ፍሬሽ ተማሪዎች ጋር የሚስተዋለው ስህተት ደግሞ ብሄር ነክ ግጭቶችን ማድረግ ነው።

በተለይ ማንኛውንም አለመግባባት በፍጥነት ወደ ሌላ መልክ ለመቀየር የሚሞክሩ ተማሪዎችን እያስተዋልን ነው።

ነገር ግን የዩኒቨርስቲ ግቢ ሺዎች በጋራ የሚኖሩበት ግቢ በመሆኑ ትልቅ መቻቻል እና ትዕግስት መላበስ መቻል ግድ ነው።

#ከሰላምታ_ጋር
የወ/ዩ/የተ/ህ/ፅ/ቤት

ትምህርት ሚኒስቴር
@MINISTERY_OF_EDUCATION
75.9K viewsHENOK, 18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2018-12-30 21:06:33 አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ አባል ሆነዉ ተሰየሙ፡፡

ክብርት ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል በሰብሳቢነት እና ኢንጂነር ታከለ ኡማ በምክትል ሰብሳቢነት መሰየማቸዉ ይታወሳል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር
  @MINISTERY_OF_EDUCATION
72.7K viewsHENOK, 18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2018-12-22 12:27:13 ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ

በከተማው ህበረተሰብ እና በዩኒቨርሲቲው አስተዳደር መካከል በጠፈጠረዉ አለመግባባት የዩኒቨርሲቲው እሰካሁን ተማሪዎችን መቀበል አልቻለም በዚህም መሰረት ትምህርት ሚኒስቴር የስራ ባልደረቦቹን ልኮ ባካሄደዉ ጥልቅ ስበሰባ በህበረተሰቡ እና ዩኒቨርሲቲው መካከል ያለዉን ችግር ተፈቷል።

ይሄን ተከትሎ ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችን ከየካቲት ወር መጀመሪያ ጀምሮ ተቀብሎ ለማስተማር ዝግጅት የጀመሩ ስሆን ተማሪዎችም ዝግጁ ሆናችሁ የዩኒቨርሲቲው ጥሪ እንድትጠባበቁ እናሳስባለን።

ትምህርት ሚኒስቴር
 @MINISTERY_OF_EDUCATION
71.6K viewsHENOK, 09:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2018-12-21 15:43:06 #ማስታወቂያ

በ2011 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር ወደ ራያ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ተማሪዎች በሙሉ ዩኒቨርሲቲው በታህሳስ 24 እና 25 ፣2011 ዓ.ም ተማሪዎችን የሚቀበል መሆኑን እያሳወቀ ሁላችሁም ተማሪዎች
1. 12 ጉርድ ፎቶ ግራፍ
2. ስምንተኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ስርትፍኬት
3. የ9ኛ እና የ10ኛ ክፍል ትራንስክርቢት
4. የ10ኛ ክፍል የሃገራዊ ፈተና ውጤት
5. የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ትራንስክርቢት
6. የ12ኛ ክፍል ሃገራዊ ፈተና ውጤት
7. አንሶላና ብርድ ልብስ በመያዝ ከላይ በተጠቀሱት ቀናት በዩኒቨርሲቲው ግቢ ተገኝታችሁ እንድትመዘገቡ እያሳሰብን ከተጠቀሱት ቀናት በፊትም ሆነ በኋላ የሚመጡ ተማሪዎችን የማናስተናገድ መሆናችንን እናሳውቃለን፡፡
የራያ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት
ሳይንስ ለተሻለ ህይወት

ራያ ዩኒቨርስቲ

@MINISTERY_OF_EDUCATION
68.9K viewsHENOK, 12:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2018-12-21 15:34:57 የሴት አመራሮች ተሳትፎ

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘውን የሴት አመራሮችን ተሳትፎና ብቃት ለማሳደግ ለሚያስችሉ ስራዎች ትኩረት ተሰጥቶ በመስራት ላይ መሆኑን ክብርት የኢፌዲሪ ሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶክተር ሒሩት ወልደማርያም አስታወቁ፡፡

የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትሯ ዶክተር ሒሩት ወልደ ማርያም ከአገሪቱ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከተውጣጡ ሴት የስራ ኃላፊዎች፣ ሴት ሙሁራንና ተመራማሪዎች ጋር ውይይት ባደረጉት ወቅት እንደገለጹት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ ሴት ሙሁራንና ተመራማሪዎች ተገቢ ቦታቸውን እንዲያገኙ እየተሰራ ይገኛል፡፡

የከፍተኛ ትምህርት አመራር የመመልመያ መመሪያን በመከለስ በዩኒቨርስቲዎች ቢያንስ ሁለት ከፍተኛ አመራሮች እንዲቀመጡ በማድረግ ተሳትፎአቸውን የበለጠ ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ሚኒስትሯ አስረድተዋል፡፡

በዚህም መሠረት አስራ ስምንት ሴት ሙሁራን በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ወስጥ በምክትል ፕሬዚዳንትነት በማገልገል ላይ እንደሚገኙ ጠቁመው የቦርድ አመራር ስምሪቱንም በማሻሻል በአሁኑ ሰዓት ከመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የቦርድ አመራሮች መካከል ሦስቱ ሴቶች መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡

የሴት ሙሁራንና አመራሮች ተሳትፎ እያደገ ቢሆንም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአመራርነትና በመማር ማስተማር ሥራ ተሳትፎ በማድረግ ላይ ከሚገኙ ሴት ሙሁራን መካከል የፒኤች ዲ ወይም ሦስተኛ ዲግሪ ያላቸው ሴቶች ቁጥር አሁንም ከአስር በመቶ እንደማይበልጥ ዶክተር ሂሩት ተናግረዋል፡፡

ሴት አመራሮች ወደ አመራርነት በከፍተኛ ደረጃ እየመጡበት ያሉበት ወቅት በመሆኑ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሚገኙ ሴት ሙሁራን ምቹ ሁኔታ በመፍጠር በላቀ ደረጃ ወደ አመራርነት እንዲመጡ በሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል በጋራ መስራት እንደሚገባም ክብርት ሚኒስትሯ አስገንዝበዋል፡፡

በመድረኩ የተሳተፉ የሁሉም የከፍተኛ ትምህርት አመራር ሴቶች ያቀረቧቸው ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶችም በክብርት ሚኒስትሯ ማብራሪያና ምላሽ የተሰጠባቸው መሆኑን የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዘግቧል፡፡
     ትምህርት ሚኒስቴር
  @MINISTERY_OF_EDUCATION
67.6K viewsHENOK, 12:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2018-12-21 15:34:53 ዝርዝር........

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ #ሠላማዊ በሆነ ሁኔታ ላይ ይገኛል።

በአለፉት ሦስት ቀናት በተወሰነ ተማሪዎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የመማር ማስተማሩ ስራ እንደተስተጓጎለ ይታወቃል፡፡

በእዚህ ላይ የእርምት እርምጃ ለመውሰድ ከአካባቢው ማህበረሰብና ከተማሪ ተወካዮች ጋር የተለያዩ ውይይቶች እየተደረጉ ይገኛሉ፡፡

ዩኒቨርሲቲውም በተማሪዎች የሚነሱ ጥያቄዎችን ምላሽ ለመስጠት ጠንክሮ እየሰራ ይገኛል፡፡

አሁን ላይ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ያለው የተማሪዎቻችንን ሠላምና ደህንነት ማስጠበቅ ላይ ነው፡፡ በእዚህም ምክንያት ተማሪዎቻችን እንደሰጋት የሚያነሷቸውን የደህንነት ጥያቄዎች አስተማማኝ ለማድረግ ተጨማሪ የፌዴራል ኃይል በመጨመር የግቢው ጥበቃ የተጠናከረ እና አስተማማኝ እንዲሆን ተደርጓል፡፡

በነገው እለት የጋራ መስማማት ላይ ለመድረስና ትምህርት ለማስጀመር ከግቢ ከወጡ ተማሪዎች ጋር ውይይት ይደረጋል፡፡ በእዚሁ አጋጣሚ ሁሉም ሊረዳ የሚገበው የዩኒቨርሲቲው ፀጥታ ፍፁም አስተማማኝ መሆኑን ነው፡፡

@MINISTERY_OF_EDUCATION
63.7K viewsHENOK, 12:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ