#ሕፃን_መፃጕዕ (ውርስ ትርጉም) ከሣቴብርሃን ገብረኢየሱስ @Mgetem “ብላቴና” የሚል፤ ከግብሩ የተነሣ የተሰጠው ቅፅል፤ በትርጓሜ ወንጌል የሚነበብ ሰፍሮ፤ መፃጕዕ መፃጕዕ ሕፃነ አእምሮ፤ ጨቅላ ነው ፤ ትክክል! ምንም ነፍስ የማያውቅ፤ እሳትና ውሃን መለየት የማይችል። ቢለይማ ኖሮ፤ ከእሳተ መለኮት ፤ እጁን ይልክ ነበር ፤ ለጥፊ ሰንዝሮ ? ...................................................... መነሻ ቅኔ ፦ ዕዝል ጉባዔ ቃና ዘመሪጌታ ጥበበ ደስታ ሕፃን ኢያእመሬ ነፍስ ዓዲ፤ አኮኑ ፈነወ እዴሁ መንገለ እሳት ነዳዲ ....................................................... መፃጕዕ ለ 38 ዓመት ሲማቅቅበት ከነበረ ደዌው የፈወሰው ክርስቶስን በቤተመቅደስ በጥፊ ስለ መምታቱ መሪጌታ ጥበበ ደስታ የተቀኙትን ቅኔ መነሻ በማድረግ የተገጠመ ከሣቴብርሃን ገብረኢየሱስ ....................................................... @Mgetem @Mgetem @Scgpx9 1.4K viewsKesatebirhan, 05:10