2021-09-01 19:43:58
ርዕስ ፦በእግዚያብሄር ፈቃድ ውስጥ መኖር
ማቴ፦፯፥፳፩
በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግስተ ሰማያት የሚገባ አይደለም።
ይህ ማለት አንድ ሰው የጌታ ደቀ መዝሙር ነው የሚባለው ደግሞም መንግስተ ሰማይ የሚገባው የእግዚያብሄርን ፈቃድ ሲያደርግና በዚህ ፈቃድ ውስጥ ሲኖር ነው።
ኤፌ ፪፦፩-፪
በፊት ስንመላለስ የነበርንበትን ሲገልፅ
በበደላችሁና በኃጢያታችሁ ሙታን ነበራችሁ በእነርሱም በዚህ ዓለም እንዳለሁ ኑሮ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሰራው መንፈስ አለቃ እንደሆነው በአየር ላይ ስልጣን እንዳለው አለቃ ፈቃድ በፊት ተመላለሳችሁባቸው።
ስለዚህ መንግስተ ሰማይ የሚገባ ሰው የራሱንና የዚህ ዓለም ገዢን ፈቃድ ትቶ በእግዚያብሄር ፈቃድ ውስጥ የሚኖር ነው እንጂ ትንቢት የሚናገር ፣የሚዘምር፣ ፓስተር፣ፈቃዱን ሳይሰጥ ገንዘብ የሚሰጥ ከቶ አይደለም።
በእግዚያብሄር አምናለሁ ስለዚህ እገባለሁ የሚል ሰው አይጠፋም ሰለዚህ ሀሳብ ያዕቆብ ሲናገር
ያቆ፦፪፩፥፩፱
እግዚያብሄር አንድ እንደሆነ ታምናለህ መልካም ታደርጋለህ አጋንንትም ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል ይላል።
በዘመረ፣በሰበከ፣ትንቢት በተናገረ ፣አምኖ ብቻ በተቀመጠ እና አስራት በሰጠ ሳይሆን ለእግዚያብሄር ፈቃድ በኖረ ነው።
ስለዚህ በእግዚያብሄር ፈቃድ ውስጥ እንድንኖር ፈቃዱን እንድናደር ጌታ ይርዳን።
አሜን
ማቴ፦፮-፯ እንታነቡት ይሁን ተባረኩ
2.0K views16:43