2022-08-11 20:40:03
ያዕቆብ ያየሽ መሰላል አንቺ ነሽ
ያዕቆብ የአብርሐም ልጅ ነው። ያዕቆብ የስሙ ትርጉም "ተረከዝ ያዥ" ማለት ነው ። የወንድሙን እግር ይዞ ከማሕጸን ስለወጣ። ዘፍ. 25 ከወንድሙ በነበረው ጠብ ከሶርያ ምድር ተነስቶ ሸሸ። ያዕቆብ ከወንድሙ ተጣልቷል፣ አባቱን አታልሎ ብኩርናን ተቀብሏል። በመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜ ውስጥ እጅግ ደስ ከሚያሰኙት ምስጢራዊ ትርጉሞች ከተተነተኑት መካከል ያዕቆብ በሕልሙ ያየው መሰላል አንዱ ነው።
ያዕቆብ ከሶርያ ተነስቶ ሲሔድ ሎዛ ሲደርስ በመንገድ ሳለ ፀሐይ አዘቅዘቀች፤ ያዕቆብም የቀን ጉዞውን ድካሙን ሊከፍል ድንጋይ ተንተርሶ ተኛ። ያዕቆብ አስደናቂውን ሕልም ተመለከተ። ይኽ የያዕቆብ ሕልም እጅግ አስገራሚና በቀደምት ሊቃውንትም ጥልቅ ምስጢርና ትንታኔ ተሰጥቶበታል።
ያዕቆብ ያየው ድንጋይ ተንተርሶ ሲሆን ተዘርግቶ ያየው መሰላል ከምድር እስከ ሰማይ ይደርስ ነበር። በመሰላሉ ከላይኛው ጫፍ እግዚአብሔር አለበት። በመሰላሉ መላዕክት ይወጡበት ይወርዱበት ነበር። "ሕልምም አለመ፤ እነሆም መሰላል በምድር ላይ ተተክሎ፥ ራሱም ወደ ሰማይ ደርሶ፥ እነሆም የእግዚአብሔር መላእክት ይወጡበት ይወርዱበት ነበር። እነሆም፥ እግዚአብሔር በላይ ቆሞበት ነበር" ይላል። ዘፍ. 28:12
ይኽንን ቃል ከጥንታውያኑ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት እንዴት እንደተረጎሙት እንመልከት፡-
አርጌንስ (Origen)፦ ዘፍጥረትን በተነተነበት መጽሐፉ ያዕቆብ ምዕመናንን ሲወክል መሰላል በመንፈሳዊ ሕይወት ያለን እድገት ያሳያል ይላል። ይኽንን ሲያብራራም መሰላል ደረጃ እንዳለው ሁሉ ክርስትናም እንዲሁ እያደገ የሚሔድ ነው ይላል። ምጽዋት ስትሰጥ መሰላሉ በአንድ ደረጃ ከፍ ይላል። ቤተ ክርስቲያን ሔደህ ምስጢራትን ስትፈጽም መሰላሉ በአስር ደረጃ ከፍ ይላል ብሎታል። Gregory of Nazianzus, Homily n. 43 (Funeral Oration on the Great S. Basil), 71
ይኽንን ኅሳቡን የሚጋራው ቅዱስ ጄርምም በጎ ምግባራት ባደረግህ ጊዜ እንዲሁ ወደ ላይ (ወደ እግዚአብሔር) ማደግ ትጀምራለህ። አርጌንስ ይቀጥልና ምግባርን እየጨመርክ በሔድክ ጊዜ ብርሃን ወደሆነው እግዚአብሔር እየተጠጋን ነው። ከሞት በኋላም የነስፍ እድገቷ አይቆምም ይለናል።
ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ሲናገር ይኽ መሰላል ወደ ላቀ መንፈሳዊነት ማደግን በተለይም በተባሕትዎ (Asetic life) መኖርን ያሳያል ሲል፤ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅዱስ ጳውሎስን አብነት እድርጎ ደግሞ መሰላሉ በሰው እጅ ባልተሰራችው ሰማያዊ ቤተ መቅድስ የሚያደርስ ነው ይለናል። Gregory of Nazianzus, Homily n. 43 (Funeral Oration on the Great S. Basil), 71
የሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሶርያዊው አፍርሐት የተባለው በተለይ በነገረ ማርያም ላይ ሰፊ ጽኁፍ በመጻፉ ሲታወቅ በተለይም ፡ ዓይነ ልብ ( the luminous eye)በሚባለው ጽኁፉ እናውቀዋለ። ይኽንን መሰላል ሲተረሩም መሰላል የክርስቶስ መስቀል ነው ይላል። “the ladder of Jacob’s dream symbolizes the cross of Christ” ይህውም መስቀል ከታች ከምድር (ከውድቀት) ወደላይ ወደሰማይ (ወደ እግዚአብሔር) አድርሶናል። በማለት አመስጥሮታል።
የቅርብ ጊዜያት የነገረ መለኮት ምሑራን (contemporary theologian) በመጀመሪያ እግዚአብሔር ያዕቆብን ያስተማረው ከራሱ ሕይወት በመነሳት ነው። ይኽውም ወንድሙን አታሎ፣ አባቱን ዋሽቶ ነው የመጣው ስለሆነ ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ግንኙነትን አሻክሮ ነበር ። ስለሆነም እግዚአብሔር መንገዱን እንዲያስተካክል ነው የነገረው። ያዕቆብም መንገዱን ቃል በመግባት አስተካክሏል። ይህም የተነሳሂን ሕይወት ያሳያል ብለውታል።
የያዕቆብ ሕልም የሕይወቱ መቀየሪያም ክስተት ነበር። እግዚአብሔርንም ለማገልገል ቃል የገባበት ነበር። ለያዕቆብም የተነጋገረው እግዚአብሒር ለኃጢአቶኞች አዛኝ እና ይቅር ባይ መሆኑን አሳይቷል ይላሉ። (sacred symbols that speak p 62)
አውግስጢኖስም (Augustine) መሰላልን በተለየ መልኩ ሲያብራራ መሰላል ቤተ ክርስቲያን ናት ይላል። (lecture or tractate st. john, tractate 7)
ቅዱስ ጄሮም ይቀጥልና ያዕቆብ የተንተራሰው ድንጋይ ክርስቶስ ነው ይለናል። ይኽንንም መጽሐፍ ቅዱስ በመዝሙረ ዳዊት የተነገረው ትንቢት በጌታም ትምህርት እንዲሁም በሐዋርያት ስብከት በተደጋጋሚ ስለ ማዕዘን ራስ ድንጋይ ተነግሯል " ግንበኞች የናቁት ድንጋይ፥ እርሱ የማዕዘን ራስ ሆነ" እንደተባለ። መዝ.118፡22 ማቴ.21፡42
የማዕዘን ራስ ድንጋይ ዋና ዓላማው የቤቱን ላይና ታች አጋጥሞ ማቆም ነው። የተጣላውን የሰውን ዘር ከእግዚአብሔር ጋር አስታርቆ አንድ አድርጓልና። ቅዱስ ጴጥሮስንም ስለ ጌታ በመሰከረው ትምሕርት "እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም። በማለት አለትነቱን አረጋግጦልናል" ማቴ 16፡ 18
የቢዛንታይን ቤተ ክርስቲያን አባቶች የያዕቆብ መስላል እመቤታችን ናት በማለት ይተረጉማሉ። ይኽንን ትርጉም ሁሉም ኦርቶዶክሶች ይስማማሉ ። ቅዱስ ኤፍሬም በማክሰኞ ውዳሴ ማርያም ላይ "አንቺ የያዕቅብ መሰላል ነሽ" ይላታል።
"አንቲ ወእቱ ሰዋስው ዘርእየ ያዕቆብ እምድር ዘይበጽሕ አስከ ሰማይ" ከምድር እስከ ሰማይ ተተክላ መላዕክት ሲወጡባት ሲወርዱባት ያዕቆብ ያያት መሰላል አንቺ ነሽ አላት። ይኽም መሰላል የወርቅ ነው ምሳሌውም ቅድስናዋን ንጽሕናዋን ያመለክታል።
ከምድር እስከ ሰማይ መድረሱ አምላክን እና ሰውን ያገናኘች መሰላል (ቃል ሥጋ የሆነባት) መሆኗን ያመለከታል። ያዕቆብ የተንተራሰው ድንጊያ የእመቤታችን በትንቢተ ነቢያት ጸንታ መገኘቷን። አምላክ ሰው ከሆነ በኋላ መላዕክት ለምስጋና ለተልእኮ የሚወጡ የሚወርዱ መሆናቸው አሳይቷል በማለት ያብራራዋል። (ውዳሴ ማርያም ትርጉም)
አምላክ ሰው ሆነ ሰው አምላክ ሆነ ብለው መውጣት መውረዳቸውን አስረጅ ነው። ጌታችንም ለናትናኤል "እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይ ሲከፈት የእግዚአብሔርም መላእክት በሰው ልጅ ላይ ሲወጡና ሲወርዱ ታያላችሁ አለው" ብሎታል። ዮሐ. 1፡52
እመቤታችን ሰውና አምላክን ያገናኘች መሰላል ስትሆን የሰውን ልጅ በምልጃዋ ወደ እግዚአብሔር በማቅረብ ወደ መንግስተ ሰማይ የሚገቡበትን ጸጋ ያገኛሉ። ድንግል ሆይ አንቺ መስለላላችን ነሽ።
ለጥልቅ ንባብ Ancient , Christian commentary on scripture old testament vol 2 p 186
የእመቤታችን አማላጅነት አይለየን
መ/ር ንዋይ ካሳሁን
https://t.me/akanim1wasen2
828 viewsወሰንየለው ባህሩ, 17:40