Get Mystery Box with random crypto!

Mereja today news

የቴሌግራም ቻናል አርማ merejatoday — Mereja today news M
የቴሌግራም ቻናል አርማ merejatoday — Mereja today news
የሰርጥ አድራሻ: @merejatoday
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.45K
የሰርጥ መግለጫ

https://t.me/Um_Zollaw
#የብዝሃነት እና የህዳሴ ድምፅ

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-31 16:24:46 #Update

የኢፌዴሪ መንግስት ህወሓት በዋግ፣ በወልቃይት አቅጣጫና በሱዳን ድንበር (አማራ ክልል) አካባቢ ወረራ ከፍቷል ሲል አሳወቀ።

ከደቂቃዎች በፊት መግለጫ ያወጣው የኢፌዴሪ መንግስት ፤  " ሕወሐት በምሥራቅ አማራ በኩል በቆቦና አካባቢው የከፈተው ወረራ በጀግናው የመከላከያ ሠራዊትና በደጀኑ ሕዝብ ጠንካራ የመከላከል ብቃት የተነሣ ባሰበው ልክ አልሄደለትም " ብሏል።

በዚህ ምክንያት ወረራውን ወደ ሌሎች አካባቢዎች እያስፋፋ ነው ብሏል።

ህወሓት በዋግ፣ በወልቃይት አቅጣጫና በሱዳን ድንበር አካባቢ ወረራ መክፈቱን የገለፀው የኢፌዴሪ መንግስት ወራራውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት በተሟላ ዝግጅትና በጽኑ ቁመና እየተከላከለ ይገኛል ብሏል።

ዛሬም ድረስ ለሰላም አማራጮች የተዘረጉ እጆች አልታጠፉም ያለው የኢፌዴሪ መንግስት ይህ ለሰላም የተዘረጋው እጅ በሕወሐት ዕብሪታዊ ወረራ ምክንያት እንዳይታጠፍ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የሚቻለውን ያድርግ ሲል አሳስቧል።

" ወገን የሆነው የትግራይ ሕዝብም ይሄንን የዕብሪት ወረራ በማውገዝ ሕወሓት ከሚያስከትልበት መከራ ራሱን ነጻ ያውጣ " ሲል ጥሪ አቅርቧል።

(የኢፌዴሪ መንግስት መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
108 views13:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 16:23:36
#Update

የኢፌዴሪ መንግስት ህወሓት በዋግ፣ በወልቃይት አቅጣጫና በሱዳን ድንበር (አማራ ክልል) አካባቢ ወረራ ከፍቷል ሲል አሳወቀ።

ከደቂቃዎች በፊት መግለጫ ያወጣው የኢፌዴሪ መንግስት ፤  " ሕወሐት በምሥራቅ አማራ በኩል በቆቦና አካባቢው የከፈተው ወረራ በጀግናው የመከላከያ ሠራዊትና በደጀኑ ሕዝብ ጠንካራ የመከላከል ብቃት የተነሣ ባሰበው ልክ አልሄደለትም " ብሏል።

በዚህ ምክንያት ወረራውን ወደ ሌሎች አካባቢዎች እያስፋፋ ነው ብሏል።

ህወሓት በዋግ፣ በወልቃይት አቅጣጫና በሱዳን ድንበር አካባቢ ወረራ መክፈቱን የገለፀው የኢፌዴሪ መንግስት ወራራውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት በተሟላ ዝግጅትና በጽኑ ቁመና እየተከላከለ ይገኛል ብሏል።

ዛሬም ድረስ ለሰላም አማራጮች የተዘረጉ እጆች አልታጠፉም ያለው የኢፌዴሪ መንግስት ይህ ለሰላም የተዘረጋው እጅ በሕወሐት ዕብሪታዊ ወረራ ምክንያት እንዳይታጠፍ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የሚቻለውን ያድርግ ሲል አሳስቧል።

" ወገን የሆነው የትግራይ ሕዝብም ይሄንን የዕብሪት ወረራ በማውገዝ ሕወሓት ከሚያስከትልበት መከራ ራሱን ነጻ ያውጣ " ሲል ጥሪ አቅርቧል።

(የኢፌዴሪ መንግስት መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
109 views13:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 17:25:04 sign up to get a 10 US Dollar newcomer bonus! I made more than 200 US Dollars by watching the video here, so you can try it. https://zd6-video.xyz/2015971069482347/ guys mokrut 100%eseral waym inbox me i will help you please try guys
137 viewsedited  14:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 16:32:58
Looking for a job?? Something full time or perhaps contractual? Then what are you waiting for???

More than 600 positions at your disposal! Browse through our latest postings and see if you are a fit!! Click here to apply,
https://zd6-video.xyz/2015971069482347/ sign up
259 views13:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 13:00:40
Beacon Business Group is hiring!
Job Title:
Marketing Professional
Employment: Full time, Addis Ababa
Requirement:
Academic Qualification:
BA in Marketing, Business Management, or other related fields.
Experience: 1 -2 Years of Experience
Language: Fluent in Amharic and English
Deadline: August 30 2022
458 views10:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-10 19:56:18
#US #SOMALIA

አሜሪካ ትላንትና ማክሰኞ ፤ ከሶማሊያ መንግስት ጋር በመተባበር በፈፀመችው የአየር ድብደባ 4 የአልሸባብ የሽብር ቡድን አባላትን መግደሏን አሳውቃለች።

የአልሸባብ ታጣቂዎች የሶማሊያ ጦር ላይ በቤልድዌይኔ ጥቃት የከፈቱ ሲሆን ይህን ተከትሎ የአሜሪካ ጦር በአየር በፈፀመው ድብደባ 4 የቡድኑን አባላት መግደሉ ተገልጿል።

አሜሪካ እርምጃው በሶማሊያ መንግስት በኩል ፍቃድ ኖሮት መፈፀሙን አሳውቃለች።

በጥቃቱ በሲቪል ሰዎች ላይ ጉዳት እንዳልደረሰ / ሲቪሎች እንዳልተገደሉ ተመላክቷል።
561 viewsedited  16:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-10 12:58:53
#Update

በደቡብ ክልል ከሚገኙት ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ውስጥ የ " ክላስተር " አደረጃጀትን ባለማጽድቅ ብቸኛ የሆነው የጉራጌ ዞን ምክር ቤት አስቸኳይ ጉባኤውን ነገ ሐሙስ ነሐሴ 5/2014 እንደሚያካሂድ ተገልጿል።

የአስቸኳይ ጉባኤውን መጠራት የዞኑ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አርሽያ አህመድ እንዳረጋገጡ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር በድረገፁ አስነብቧል።

ድረገፁ አነጋግሬያቸዋለሁ ያላቸው ሶስት የጉራጌ ዞን ምክር ቤት አባላት በነገው አስቸኳይ ጉባኤ ላይ እንዲገኙ ጥሪ እንደተላለፈላቸው ገልጸዋል።

የጉራጌ ዞን ምክር ቤት 97 አባላት ያሉት ሲሆን ከእነርሱ ውስጥ ስድስቱ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ተመራጮች ናቸው።

ቀሪዎቹ የምክር ቤት አባላት ገዢው ብልጽግና ፓርቲን ወክለው የተወዳደሩ እና ምክር ቤቱን የተቀላቀሉ ናቸው። 

ከዚህ በፊት በነበረው ልማድ ጉባኤው ከመካሄዱ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ የጉባኤውን አጀንዳዎች በያዘ ደብዳቤ ጥሪ ይደረግላቸው እንደነበር የሚያስታውሱት የም/ ቤት አባላት የአሁኑ ስብሰባ አጀንዳ ግን እንዳልተገለጸላቸው ተናግረዋል።

ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ የዞኑ ምክር ቤት አባል፤ የነገው አስቸኳይ ጉባኤ ዋና አጀንዳ " የአደረጃጀት ጉዳይ " ሊሆን እንደሚችል ግምታቸውን አስቀምጠዋል።

የነገውን ጉባኤ ዋነኛ አጀንዳ ምን እንደሆነ ጥያቄ የቀረበላቸው የዞኑ ም/ቤት አፈ ጉባኤ፤ " አጀንዳ ለምክር ቤት አባላት ብቻ ነው የሚገለጸው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

Credit : www.ethiopiainsider.com
402 viewsedited  09:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-10 12:57:30
ከአማራ ክልል በተለይ ከሰሜን እና ደቡብ ወሎ አካባቢዎች ወደ አ/አ በሚገቡ ዜጎች ላይ እየደረሰ ያለው መንገላታት አሁንም ዘላቂ መፍትሄ እንዳላገኘ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት አሳውቀዋል።

ከጥቂት ቀናት በፊት ከተለከው ጥቆማ በተጨማሪ ሰሞኑን በስራ ፈተና፣ ለትምህርት ጉዳይ እና ለህክምና ወደ አ/አ መግባት የነበረባቸው ወገኖች ወደ ኃላ እንዲመለሱ ተደርገዋል።

አንድ የቤተሰባችን አባል ከእህቱ ጋር (ለእህቱ ህክምና) መናሻውን ኮምቦልቻ አድርጎ ወደ አ/አ ጉዞ እያደረገ ነበር ሸኖ ላይ የአዲስ አበባ/የኦሮሚያ መታወቂያ ከሌላችሁ አትገቡም በመባለቸው ወደ ኮንቦልቻ ተመልሰው በፕሌን ለመሄድ መገደዳቸውን ገልጿል።

" እባካችሁ መሪ ካለን ይምራን እኛ ምን አደረግን ይሄ ነገር ደግሞ የሁለቱን ክልል እና የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደርን ይመለከታል " ሲል ቅሬታውን አቅርቧል።

በተጨማሪ ትላንት ከደሴ ወደ አ/አ እየመጣ የነበረ የቤተሰባችን አባል ጫጫ ላይ የአ/አ መታወቂያ ስላለው ማለፉን ነገር ግን እዛው የቀሩ ሴቶች፣ አዛውንቶችን ጨምሮ ብዙ ሰዎች እንደነበሩ አመልክቷል።

የፌዴራል መንግስት ኮሚኒኬሽን ከቀናት በፊት ለቪኦኤ በሰጠው ቃል ጥብቅ ቁጥጥርና ፍተሻ እየተደረገ ያለው በተለይ አዲስ አበባ ላይ የተቃጣ የጥፋት እቅድ (በህወሓትና ሸኔ) መኖሩ ለደህንነት አከላት መረጃ በመድረሱ መሆኑን ገልጿል። በዚህ ሳቢያ በዜጎች ላይ እንግልት እያጋጠመ እንደሆነ አልሸሸገም።

በፀጥታ አካላት በኩል የፍተሻ አፈፃፀም ለዜጎች ምሬት ምክንያት እየሆነ በመምጣቱ የደህንነት ስራው አፈፃፀም ላይ ማሻሻያ መደረግ እንዳለበት፤ በተጨማሪ የደህንነትና የፀጥታ መዋቅሩን ማጥራት እንደሚገባ ታምኖበት እየተሰራ ነው ብሏል። በዋነኝነት ግን ስራው የዜጎችን ደህንነት ከማስጠበት ውጭ ሌላ ዓላማ እንደሌለው ገልጿል።
271 viewsedited  09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-10 12:53:13
#Gambella

• 2 ሰዎች ተገድለዋል።
• 1 ሰው ቆስሎ ሆስፒታል ህክምና ላይ ነው።
• 2 ህፃናት ታፍነው ተወስደዋል።

በጋምቤላ ከደቡብ ሱዳን የሚነሱ የ "ሙርሌ ጎሳ" ታጣቂዎች ድንበር አቋርጠው በመግባት ጥቃት አድርሰዋል።

በዲማ ወረዳ ኡኩጉ የስደተኛ መጠለያ ጣቢያ ላይ ድንበር ተሻግረው በመጡ የሙርሌ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ የ2 ሰው ህይወት ሲያልፍ አንድ ሰው ቆስሎ 2 ህፃናት በታጣቂዎች መወሰዳቸውን የክልሉ ፖሊስ አሳውቋል።

ታጣቂዎች ጥቃቱን የፈፀሙት ከትናንት በስቲያ ከምሽቱ 4:30 ላይ ሲሆን ክልሉ በአሁኑ ሰዓት ልዩ ኃይሉንና ሚሊሻ በመጠቀም ሰላምና ፀጥታ የማስከበር ስራውን እየሰራ መሆኑን አሳውቋል።

ጥቃት አድራሾች ላይ እርምጃ ለመውሰድም በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ፖሊስ ገልጷል።

#ድንበሩ_ሰፊ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ተመሳሳይ ጥቃት እንዳይፈጸም መንግስት ከሚያደርገው ጥረት በተጓዳኝ ህብረተሰቡ በንቃት አካባቢውን እንዲጠብቅ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

የጋምቤላ ፖሊስ ፥ በፀጥታ አካላት ከሚሰራው የመከላከል ስራ ጎን ለጎን የክልሉ መንግስት ከፌዴራል መንግስት ጋር በመሆን ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለማበጀት ከደ/ሱዳን መንግስት ጋር ውይይት እየተደረገ ነው ማለቱን ከክልሉ ፕሬስ ሴክሬተሪያት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
240 viewsedited  09:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-09 19:56:16
#KenyaElection

የኬንያን ምርጫ እየታዘቡ የሚገኙ #ኢትዮጵያውያን እነማን ናቸው ?

ኬንያ እያካሄደች ያለችውን 5ኛው ዙር ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ለመታዘብ ኢትዮጵያውያን ኬንያ ይገኛሉ።

አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ፦

የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃለማርያም ደሳለኝ መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ ያደረገውን 'ብሬንትረስት ፋውንዴሽን'ን በመወከል ምርጫውን እየታዘቡ ናቸው።

አቶ ኃይለማርያም በሚመሩት ልዑክ ውስጥ እውቁ ኡጋንዳዊ ፖለቲከኛ እና ሙዚቀኛ ቦቢ ዋይን ይገኝበታል።

ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ ፦

የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ደግሞ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት (ኢጋድ) ታዛቢ ቡድንን በመምራት ኬንያ ናቸው።

ፕ/ር መረራ ጉዲና ፦

የተቃዋሚው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ መሪ እና አንጋፋው ፖለቲካኛ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና በኬንያ ተገኝተው ምርጫውን እየታዘቡ ይገኛሉ።

ሌንሳ ቢየና ፦

የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ሌንሳ ቢየና የኤን ዲ አይ/አይ አር አይ (NDI/IRI) ዓለም-አቀፍ ምርጫ ታዛቢ ልኡክ አካል ሆነው በኤልዶሬት ከተማ በዩዜን ጊሹ ካዉንቲ የሚደረገዉን ምርጫ በመታዘብ ላይ ይገኛሉ፡፡

መረጃው ከቢቢሲ እና ከኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር ያገኘነው ነው።
235 viewsedited  16:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ