Get Mystery Box with random crypto!

መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

የቴሌግራም ቻናል አርማ menfesawigetmoch — መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
የቴሌግራም ቻናል አርማ menfesawigetmoch — መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
የሰርጥ አድራሻ: @menfesawigetmoch
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.32K

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-04-15 07:09:47
አለምን የሰራ ሲሆን፥
ከእኛ እንዳንዱ ቢሆን።
እንደ በደለኛ ቆጥረነው፥
በእንጨት መስቀል ላይ ሰቀልነው።
++++++
ታዜና
#መንፈሳዊ_ግጥሞች
t.me/Menfesawigetmoch
196 views04:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 10:50:07
++++++++++++++++++++
ሆሣዕና....
ወደ ኢየሩሳሌም፥ ቤተ ፋጌ ሲደርስ፤
የታሰረች አህያ፥
ፈተው እንዲያመጡ፥ ላካቸው ክርስቶስ።
እነዚህ ለጌታ፥ ያስፈልጋሉና፤
የታሰረችውን፥ አምጡልኝ ፍቱና።
ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ላሳየሽ በጎነት ላሳየሽ ትህትና፤
እልል በይ ዘምሪ፥ እያልሽ ሆሣዕና።

አዳኝና ትሁት፥ ፃድቅ ንጉስሽ፤
በውርንጫ ጀርባ፥ መቷል አዳኝሽ።
ዘንባባ አንጥፉ፥ ህፃናትም ውጡ፤
አሁን አድን በሉት፥ ምስጋናችሁን ስጡ።
ሆሣዕና....
ደግሞም በዚያችው ቀን፥ ከመቅደስ ገባና፤
የሻጮችን ዙፋን፥ ገለበጠውና።
የወንበዴዎች ዋሻ፥ ያረጉትን ቤቱን፤
ርግብ ሻጩን ሰዶ፥ አፀዳ መቅደሱን።
የገንዘብ ለዋጩን፥ ወንበር ገለበጠ፤
በመቅደሱ ዙፋን፥ ጌታ ተቀመጠ።

ከሚጠቡትም አፍ፥ ምስጋና አዘጋጀ፤
አምላክነቱንም፥ ለአለም አወጀ።
የምትቀድሙ የምትከተሉ፥ ሆሣዕና እያላችሁ፤
በአርያም ይሰማ፥ መዝሙር እልልታችሁ።

አቤቱ ጌታ ሆይ፥ አሁን አድን በሉት፤
ልብሳችሁን ዘርጉ፥ ዘምባባ አንጥፉለት።
አሁን አድን ብለን፥ ወተናል በመንፈስ፤
በውርንጫ ጀርባ፥ አምላካችን ሲደርስ።
የዘካርያስ ትንቢት፥ አልቀረም ተፈቷል፤
በውርንጫ ጀርባ ፥ንጉሳችን መቷል።
+++++++++++++++++++++
@Menfesawigetmoch
ታዜና
" የሚቀድሙትም የሚከተሉትም። ሆሣዕና፤ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤"
(የማርቆስ ወንጌል 11:9)
588 viewsedited  07:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-12 09:18:03 !
ጠብቅ...!
!
ተዋህዶ እምነትህን፣
ቤተክርስቲያንህን፣
የአርባ ቀን ቤትህን፣
አንዲት ስስትህን፣
የደም ስርህን፣
እናት አለምህን፣
ስም የሰጠችህን፣
ልጅ ያረገችህን።
!
ጠብቅ...!
!
አባት ካህንህን፣
የሚባርክህን፣
የሚናዝዝህን፣
ይፍታህ የሚልህን፣
ግርማ ሞገስህን፣
የሲኖዶስህን፣
የፓትሪያርክህን፣
ዶግማ ቀኖናህን፣
እምነት ማተብህን።
!
ጠብቅ...!
! አታስነጥቅ።
++++
አንድ ቤተክርስቲያን
አንድ ሲኖዶስ
አንድ ፓትሪያርክ
አንድ መንበር
++++++
ታዜና
      #መንፈሳዊ_ግጥሞች
      t.me/Menfesawigetmoch
88 views06:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-11 17:54:05 ዖዝያን....
በክብር ቢቀባ ፥በአስራ ሶስት አመቱ፤
በዙፋን ቢቀመጥ፥ ፀንቶለት ሹመቱ።
እግዚአብሔር ነገሩን፥ እየከወነለት፣
እልፍ እየማረከ፥ እልፍ ቢያስገዛለት።

በበረታ ጊዜ፥ ለጥፋት ታበየ፤
በመቅደሱ ሊያጥን፥ ጽና ይዞ ታየ።
ካህኑ የአሮን ልጅ፥ ዓዛርያስ ሳለ፤
ንግስናውን ትቶ፥ ንጉስ ልጠን አለ።

የእግዚአብሄር ፍርድ፥አይለወጥምና ፤
ተመለስ ንጉስ ሆይ፥ በዙፋንህ ጽና፤
ጽና ይዞ ማጠን፥ ያንተ አይደለምና፤
ቢለው አልሰማ አለ፥ ካህኑን ናቀና።

የትዕቢቱ መጠን፥ ዙፋኑን ነቀነቆ፤
ለየው ከንግስና፥ ካባውን አውልቆ።
ያደረገለትን ሀይል፥ ክብሩን ዘንግቶ፤
ንጉስ ልጠን አለ፥ ቤተመቅደስ ገብቶ።

እግዚአብሄር ቀሰፈው፣ ለምጽን አተመበት፤
በቤተ መንግስቱ፥ ልጁ ነገሰበት።
የማይነካ ነክቶ፥ንግስናው ተሻረ፤
ከአባቶቹ ርቆ፥ በእርሻ ተቀበረ።

ዛሬም ዖዝያን ሆይ!
በበረታህ ጊዜ፥ ጌታህን አትርሳ፤
እርሱ ነው የሚሰጥ፥ እርሱ ነው ሚነሳ።
ካህኑን አትንካ፥ የጌታን አገልጋይ፤
ቁልፍ አለና በእጁ፥ የመንግስተ ሰማይ።
++++
አንድ ቤተክርስቲያን
አንድ ሲኖዶስ
አንድ ፓትሪያርክ
አንድ መንበር
+++++
ሰማይ ስማ፥ ምድር አድምጪ፤
ቀን ወጣልኝ ብለሽ፥ ከሕጉ እንዳትወጪ።
በበደል ላይ በደል፥ እየጨመራችሁ፤
ዖዝያኖች ዛሬም፥ ትቀሰፋላችሁ።
++++++
ታዜና
      #መንፈሳዊ_ግጥሞች
      t.me/Menfesawigetmoch
465 viewsedited  14:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 19:31:41
ልባችሁ አይደንግጥ፥ አይሸበርባችሁ፣
የነገስታት ንጉስ፥ ጌታ እያለላችሁ።
ስጋን የሚገድልን፥ አትፍራ አትስጋ፣
ሰመዓትነት ነው፥ የነፍሳችን ዋጋ።
++++
አንድ ቤተክርስቲያን
አንድ ሲኖዶስ
አንድ ፓትሪያርክ
አንድ መንበር
185 viewsedited  16:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 16:02:21 አትፍራ መሞት ነው ፥ከእግዜር የሚያደርሰው፣
የእስጢፋኖስ ዘመድ ፥ነውና ምንሆነው፣
የአርሴማ ዘመድ ነውና ምንሆነው፣
የቂርቆስ ዘመድ ነውና ምንሆነው፣
የሐዋርያት ዘመድ ነውና ምንሆነው።
ዋኖቻችን ሁሉ ፥እንዲህ ነው ያለፉት፣
የክብር አክሊልን፥ በሞት ነው ያገኙት።

እናት ተዋህዶ፣ ዛሬ ትጣራለች፣
እንደ አባቶቻችን ፥ጠብቁኝ ትላለች።
++++
አንድ ቤተክርስቲያን
አንድ ሲኖዶስ
አንድ ፓትሪያርክ
አንድ መንበር
958 viewsedited  13:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 15:30:19 ዘር መሆኑን ሳያውቅ፥ የክርስቲያን ደም፣
አንዱ ወድቆ ሲሞት፥ እልፍ እንደሚቆም።
ዛሬም ይቸኩላል፥ ሄሮድስ ሊቀላ፣
አላወቀም መሰል ....
አንዱ ሞቶ ሲያድር፥ ሺህ እንደሚፈላ።
አትንኩን ብንልም፥ አንዴ ነካችሁን፣
ሰማዓትነትን ፥በመግደል ሸልሙን።
++++
አንድ ቤተክርስቲያን
አንድ ሲኖዶስ
አንድ ፓትሪያርክ
አንድ መንበር
795 viewsedited  12:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-05 23:56:17 እኔ ጥቁር እለብሳለሁ እናተስ?
ማሳሰቢያ!!!!!!!!
የነነዌ ጾም 3ቱን ቀን ከጥር 29 - የካቲት 1 ቀን ጥቁር በመልበስ ጸሎተ ምህላ እና ጸሎተ ኪዳን እያደረስን ለቤተክርስታናችን እና ለአባቶቻችን ድጋፍ እናሳይ!
ለ10 ሰው እናጋራው ለራሳችን ለህሊናችን ስንል!
937 views20:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 22:59:33
828 views19:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-30 01:34:57 ወደእኔብረሪ
በርግብ ክንፎችሽ ከአውሬው ስትሸሽ፣
በጸዳል እግሮችሽ ስትንከራተቺ
በበረሃዉ ጉያ ስትመላለሽ
ከአህያይቱ ጀርባ ጫማ ተሸክሜ
ምነው በነበርኩኝ እኔ እንደ ሰሎሜ።
ከሄሮድስ ዱላ ከሳለው ጋሻ ጦር
ፈጥነሽ እንደበረርሽ ልጅሽን ለመሰወር
እኔም እንድሰደድ ከኃጢአቴ መንደር
ለጽድቅ እንድፋጠን በሰማይ እንድበር
ደግፊኝ እመ አምላክ ክንፌ እንዳይ ሰበር።
የቀላያት ጌታ ውኃ እንደተጠማ
በነፋስ የሚበርርበ ደመናው ማማ
ውኃ ስትለምኚ ጫማ እንደተቀማ
እኔን ድርቅ ያርገኝ ከኃጢአት ልጠማ
ደረቄን እንዳልቀር ከፍሬው አውድማ።
ምድርንም ያጸና ሰማይን የታታ
ግሩም እምግሩማን ያኀያላንጌታ
ለሰው ፍቅር ብሎ ብዙ ሲንገላታ
በዉኃ እንዳጠብሽው ኃይሉ እንዲበረታ
በእንባሽ እጠቢችኝ ኃጢአቴ በርትቶ የተረታሁ ለታ።
ጸሐይንያዘልሽው ደመና መፍጠኒት
የወርቅ ሐመልማል ርግብየ ኅሪት
አክናፍኪ መስቀል የሕይወት መሠረት
ሄሮድስ ሳይውጠኝ ሳልቀሰፍ በሞት፤ወደ እኔ ብረሪ አዝለሽልኝ ምሕረት።
የግብጽን በረሃ የጎበኘሻቸው
አድባረ አግአዚትን ዞረሽ ያየሻቸው
የሕይወትን ውኃ ያዘነብሽላቸው
ሐሩሩ ሕይወቴን ፍጹሙን በረሀ
ታስትይዮ ስቴ እሴፎ አሜሃ።
ነውር የሌለብሽ መልካም ጸጌረዳ
በመንከራተትሽ ውስተ ምድረበዳ
ሸክም ቀለለልን ከፈልሽልን እዳ
በምጽአቱ ጌዜ ፍቁርሽ እንግዳ
ቅርጫፍሽ ልሁን አይብላኝ አንጋዳ።
++++
መጋቤ ብሉይ ወ ሐዲስ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
1.2K viewsedited  22:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ