2022-09-02 08:56:41
ቅዱሰ ፓትርያርኩ ሕክምናቸውን አጠናቀው ጷጉሜን ፩ ቀን ፳፻ ፲ወ ፬ ዓ.ም ወደ አገራቸውና ወደ መንበረ ክብራቸው ይመለሳሉ።
**********
ነሐሴ ፳፮ ቀን ፳፻ ፲ወ ፬ ዓ.ም
""""""""""""""""""""""""""""
አዲስ አበባ -ኢትዮጵያ
***ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ሐምሌ ፲፰ ቀን ፳፻ ፲ወ፬ ዓ.ም ወደ ሰሜን አሜሪካ በማቅናት ሕክምናቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ሕክምናቸውን በሚገባ በመከታተልና የጤናቸው ሁኔታም በመልካም ሁኔታ ላይ የሚገኝ በመሆኑ ጷጉሜን ፩ቀን ፳፻ ፲ ወ፬ ዓ.ም ወደ አገራቸው ኢትዮጵያና ወደ ቅዱስ መንበራቸው እንደሚመለሱ ታውቋል።
የቅዱስነታቸውን ወደ አገር ቤት መመለስን አስመልክቶ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የአቀባበል ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ሥራ ገብቷል።የተቋቋመው ኮሚቴ የካህናት፣የሰንበት ትምህርት ቤቶች፣የመርሐ ግብር ዝግጅትና የጸጥታ ኮሚቴዎችን ያቀፈ ሲሆን በሁሉም ዘርፍ አመርቂ ውጤት የታየበት እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል።
የአቀባበል ኮሚቴው በጠቅላይ ቤተክህነት ምክትል ዋና
ሥራ አስኪያጅ በሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን ሰብሳቢነት የሚመራ
መ/ብ አባ ተክለያሬድ ጎርጎርዮስ የሰንበት ትምህርት ቤቶት ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ
1/ መ/ሕይወት ቆሞስ አባ ኃይለገብርኤል ነጋሽ የቅዱስ ፓትርያርኩ ልዩ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ
2/ መ/ር እንቆባህርይ ተከስተ የካህናት አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ
3/ መ/ሕ ቆሞስ አባ ወልደኢየሱስ ሰይፉ የቋሚና ጊዚያዊ ፕሮጀክቶች መምሪያ ኃላፊ
4/ ወ/ሮ ጽጌረዳ አለሙ የበጀትና ሒሳብ መምሪያ ኃላፊ በአባልነት ተመድበው የተጣለባቸውን ኃላፊነት በሚገባ በመወጣት ላይ ይገኛሉ።
የኮሚቴ አባላቱ የካህናትና የሰንበት ተማሪዎች የቅድመ አቀባበል ሥራዎችን በሚገባ በማከናወን ዝግጅታቸውን አጠናቀው የቅዱስነታቸውን መምጣት እየተጠባበቁ የሚገኙ ሲሆን
ከፕሮቶኮልና ከአየር መንገድ የቪአይፒ አገልግሎት ጋር በተያያዘ ሥራውን እንዲመሩ ኃላፊነት የተሰጣቸው መ/ሕ ቆሞስ አባ ወልደኢየሱስ ሰይፉ አስፈላጊውን የፕሮቶኮል አቀባበል ሥርዓቶችን ቀድመው በማጠናቀቅ ኃላፊነታቸውን በሚገባ ተወጥተው የቅዱስ ፓትርያርኩን መምጣት በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኙ ታውቋል ይበል ብለናል ።
የበጀት፣ የመርሐ ግብር ዝግጅትና የጸጥታ ሥራዎችን እንዲሰሩ የተመደቡት ም/ል ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የቅዱስነታቸው ልዮ ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የበጀትና ሒሳብ መምሪያ ኃላፊዎች አስፈላጊውን የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ሁሉ በሚገባ ማጠናቀቃቸውም ታውቋል።
የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒዩወርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ዶ /ር አቡነ ጴጥሮስም የኮሚቴውን የሥራ እንቅስቃሴ በሚገባ በመምራትና በማስተባበር ሥራውን በአስደናቂ መልኩ ለውጤት ለማብቃት ሌት ከቀን እየደከሙ ይገኛሉ።
እግዚአብሔር ለብጹዕነትዎ
ረጅም ጊዜን ይሰጥዎ ዘንድ ጸሎታችን ነው ።
የቅዱስነታቸውን ወደ አገራቸው መመለስን በማስመልከትም የወጣቶችና ጎልማሶች ማኅበራት ሕብረት ጽርሐ መንበረ ፓትርያርኩን የቀለም መቀባት ሥራ የሙያ ሥራ ድጋፍ በማድረግ (ነጻ የጉልበት ሥራ በማከናወን) በቅዱስነታቸው ወደ መንበረ ክብራቸው መመለስ የተሰማቸውን ደስታ የሚገልጽ የበረከት ሥራ በማከናወን ላይ ይገኛሉ።
የቅዱስ ፓትርያርኩ አቀባበል መርሐ ግብር በአየር መንገድ በመገኘት እንዲቀበሉ በተፈቀደላቸው ብፁዓን አባቶች፣በጠቅላይ ቤተክህነት መምሪያ ኃላፊዎች፣በካህናትና በሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ከተከናወነ በኃላ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በምልዓተ ሕዝ ብ ይፋዊ አቀባበል እንደሚደረግላቸው የወጣው መርሐ ግብር ያስረዳል።
በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሚመራው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤም የቅዱስ ፓትርያርኩን ወደ አገራቸው መመለስን በማስመልከት ውይይት በማድረግና የአቀባበል ሥነሥርዓቱን ዝርዝር የሥራ ሒደት በማስመልከት ተወያይቶ ያሳለፈውን ውሳኔ መነሻ በማድረግ ሥራዎች በሚገባ እየተከናወኑ መሆኑም ታውቋል።
95 views05:56