Get Mystery Box with random crypto!

Memhir Girma Wondimu

የቴሌግራም ቻናል አርማ memhirgirma — Memhir Girma Wondimu M
የቴሌግራም ቻናል አርማ memhirgirma — Memhir Girma Wondimu
የሰርጥ አድራሻ: @memhirgirma
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.84K
የሰርጥ መግለጫ

<< ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል >> ወደ ቲቶ 2 ፤ 12-13
ለአሰተየታችሁ
👇👇👇👇👇👇👇
@Memhirgirma2bot

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-10-04 22:09:12 በሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ያጋጠመኝ ላካፍላችሁ ወደድኩ

ቀኑ የመስቀልን አውደ አመት ለማክበር ወደ ሀዋሳ ከተማ በከተምኩበት ጊዜ ነበር ወደ ሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን እንኳን በሰላም አስገባኸኝ ለማለት እና ለመሳለም ባቀናሁ ጊዜ
አንድ ነጭ ደመና የለበሱ የሚመስሉ
እርጅናቸው የክብር ጌጥ የሆነላቸው ገፀ-ፍቅራቸው ከሩቅ የሚጣራ መነኩሴ እናት ነፍሴን ሳቧት።

እኔም ምስጋናዬን ጨርሼ መቼም ከቤተ ክርስቲያን አዛውንት የሚገኝ በረከት ታግለው ቢፆሙ አያገኙትምና የእማሆይን በረከት ለማግኘት እግሬን አነሳሁ።

ገና ከሩቅ የሚማርኩት እማሆይ ስጠጋቸው ነገሩ ለየቅል ሆነብኝ ።
የተሸበሸበው ፊታቸው ላይ እንባ ኮለል ኮለል እያለ ይዘንባል ውስጣቸው ማዘኑን ግንባራቸው ላይ ያሳብቃል አንገታቸውን ደፍተው አንዳች ነገር ያብሰለስላሉ!

ውስጤ አንዳች ነገር ሲሰበር ተሰማኝ እጅግ ደነገጥኩ ተረበሽኩ ምን ያስብኩት በረከት ቀረና ምን እንደሆኑ ለመጠየቅ ጓጉቼ ጠጋ አልኳቸውና

እማሆይ እንዴት አሉ? አልኳቸው

እማሆይ :ሳግ በተቀላቀለው ድምፅና በተከፋ ፊት ደህና እግዚአብሔር ይመስገን አሉኝ

ምነው ምን ሆኑብኝ የተከፉ ይመስላሉ ስል አጠገባቸው ቁጭ ብዬ አቀፍኳቸው

ሆድ እየባሳቸው !! አዪ ልጄ ሰማይ ምድሩ ተደፍቶብኝ ነዋ

እኔ: ምነው እናቴ !!!

እማሆይ : አይ ልጄ

አሉኝ ማልቀስ እየዳዳቸው

እኔ: ነገሩኝ እማ ግድ የለዎትም

እማሆይ: እይውልህ ልጄ የምኖርባት የልብስ ብጫቂ የምታክል ቤት ነበረች እሷንም ተከራይቼ ነው እናም አሁን ኪራይ ከከፈልኩ 2 ወር አለፈኝ ከይት ላምጣው !!! አሁን ከየት እንደማመጣው ጨነቀኝ እንዳያስወጡኝም ሰጋሁ ቀኑ ጨለመብኝ ልጄ

አሉና አቀረቀሩ

ይህን ሲነግሩኝ ክፉኛ ልቤን ተሰማኝ ኋላም አይዞዎት እማ ይሄ ደሞ ምን ችግር አለ ብዬ
ኪሴ ውስጥ የየዛኩትን ትንሽ ብር ስስጣቸው
አዪ ልጄ!! ብለው እንቅ አረገው ሳሙኝ የምርቃት ዝናብ አዘነቡብኝ እንደ ጉድ

ያ ዳምኖ የነበረው ፊታቸው ወገግ አለ ጨልሞ የነበረው ፊታቸው ፈካ !!! በጣም ደስ አላቸው ደስ ሲላቸው ስመለከት ነፍሴ ረካች እንኳንም መጣሁ አልኩ።

እማሆይም ያ ጭንቁ ጠፍቶ ሳቅ በሳቅ አደረጉኝ አሁንማ አሉኝ እማሆይ

አሁንማ ጥርስም ባይኖረኝ እስቃለሁ አሉኝና በሳቅ አረሰረሱኝ !!!

ከዚህ በኋላ እኔ አለሁ ስላቸው በቃ ቅድም ተደፍቶባቸው የነበረው ምድርና ሰማይ አሁን በደስታ ጠበባቸው

እኔም በድስታቸው ደስ አለኝ!!!

አፉ ወርቅ የተባለለት ቅዱስ ዮሐንስ ያለው ድንቅ ቃል ትዝ አለኝ
"በቤተክርስቲያን ደጃሽ ከተቀመጡት ምስኪኖች ውስጥ ጌታን ካላገኘኸው እመነኝ ቤተመቅደሱ ውስጥ ከቅዱስ ቁርባኑ ውስጥ አታገኘው"

እውነት ነው ለካ ቤተመቅደስ ገብተን ሰላም ያጣነው እንደ እማሆይ አይነት ምስኪኖች እየገፋን ረስተናቸው ነው ።

ቆርበን ሰላም ያጣነው ቤተመቅደሱ የቅርብ እሩቅ የሆነብን እግዚአብሔርም የሸሸን ድሆችን በሩ ላይ ረስተናቸው ነው ።
የቤተ-ክርስቲያን ሊቃውንት ድሆች ማለት የመንግስተ ሰማያት መግቢያ ቁልፎች ናቸው ይላሉ

ተወዳጆች ይህን የጉዞ ማስታዎሻ ላካፍላችሁ የወደድኩት የአሳዳጁ ጀሌዎች እንደሚሉት ለታይታ አይደለም እኔ ከሁሉ ያንስኩ ጭንጋፍ ነኝ

ዳሩ ግን ተወዳጆች እናንተም ወደ ደጁ ስትሄዱ እማሆይን መሰል ብዙ የመንግስተ ሰማይ ቁልፎች አሉና ተጠቀሙባቸው ለማለት ነው ።

መፅሀፉም ለድሀ የሚሰጥ ለእግዚአብሔር ያበድራል እንዲል አሁን በየአቅጣጫው ለተደቀነብን ውስብስብ ስቃይ አንደኛው መፍቻ ውሉ ምፅዋት ነው

እማሆይ አሁን ሳቃቸው ያጠግባል ፣ ደስታቸው ያረካል ወላጅ እናቴን ጠይቄ እንደማጣሁ ተሰምቶኝ ፣ ደስታቸው ደስ አለኝ በየጊዜውም እንደምጎበኛቸውም ቃል ገብቼላቸው ወደ ቀዬዬ ተመልስኩ !!!!!!!!!!!
የኛ ጌታ የሳሮን ፅጌሬዳ ይህን እንዳደርግ ስለፈቀደልኝ ስሙ ቡሩክ ይሁን!

"ምፅዋትን በቤትህ አደልባት እርስዋም ከመከራ ሁሉ አንተን ለማዳን ትችላላች" ሲራክ 29÷12

የምትነድ እሳትን ውኃ እንደሚያጠፋት ምፅዋትም ሀጢያትን ታስተሰርያለች ፡ ምፅዋትን ለሚሰጥ ሰው በመጨረሻ ይታሰብለታል ፡ በሚሰናከልበትም ጊዜ መጠጊያን ያገኛል። ሲራክ 3÷ 28

በጎቹ" ድምፁን ይሰሙታል!

╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
✥┈┈••●◉✞◉●••┈••✥
ከመልአከ ኃይል ቀሲስ ኃይለመለኮት ግርማ ወንድሙ
18 /01/2014 ዓ.ም
ከሕይወት ተራራ ላይ መንፈሳዊነት ይብለጥ!
✥┈┈••●◉✞◉●••┈┈✥
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯
4.2K views19:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-26 17:41:24
3.1K views14:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-26 17:28:41 ✞እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም በጤና አደረሳችሁ✞

መስቀል ለማክበር በሀዋሳ ተገኝቻለሁ የጌታ ሰላም ለሁላችሁ ይሁን ።

መስቀል ቤዛችን ነው የምንለው በመስቀል ላይ የተሰራውን የቤዛነት ሥራ ነው እንጁ ዕፀ መስቀሉን አይደለም።ዕፀ መስቀሉማ በክርስቶስ ኢየሱስ ለተፈጸመልን ቤዛነት የመዳናችን ምልክት ነው። ዕፀ መስቀል በሰውና በእግዚአብሔር መካከል የነበረው የጸብ ግርግዳ በክርስቶስ ኢየሱስ ቤዛነት የፈረሰበት የነጻነት አርማችን ነው።ዕፀ መስቀል ከዲያብሎስ ቀስት የምናመልጥበት መንፈሳዊ መሣሪያችን ነው።

ስለሆነም በመስቀል ላይ ስለ እኛ ቤዛ ሆኖ የተሰዋውን በግ እያሰብን እናከብረዋለን፣ እንስመዋለን፣በመቅደሳችንም ጉልላት ከፍ አድርገን እንስቀምጠዋለን።በእጃችን ጨብጠን በአንገታችን አስረን በክርስቶስ ኢየሱስ የዳንን የተመረጠ ትውልድ ለርስቱም የተለየን ወገን መሆናችንን በማኅተባችን እንመሰክራለን።

ቤዛ ማለት ምትክ፣በሌላ ሰው ፈንታ ተላልፎ የሚሰጥ መዳኛ ማለት ነው።ስለሆነም ለክርስቲያኖች አንዱና ብቸኛው ቤዛችን የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ ክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ ነው።

መስቀሉን በየዓመቱ በልዩ መንፈሳዊ ክብረ በዓል የምናስበው የተሰቀለው በልባችን ስለ ነገሠ ነው። መስቀልና ክርስቶስ መቼም የማይነጣጠሉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው።መስቀል ብለን ስናከብር ኢየሱስን እያከበርን ነው።በኢየሱስ ደም ያገኘነውን ክብርና ነጻነትም ለዓለም እያወጅን ነው። መስቀል የነፍሳችን መዳኛ ነው ስንልም እየተናገርን ያለነው ስለ ክርስቶስ ሕማማት ነው።ምክንያቱም ለነፍሳችን ድኅነትና ጽድቅን ያገኝነው ክርስቶስ ኢየሱስ በመስቀል ላይ ሆኖ በከፈለው የሥርየት ደምና ይቅርበላቸው ብሎ ባሰማው የማስታረቅ ቃል ነው።

ተወዳጆች ሆይ ቅድስት ቤተክርስቲያናችን አንድ ጊዜ የፈሰሰው የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ዛሬም ድረስ ሕያው መታረቂያችንና መዳኛችን መሆኑን እንድናስብ ነው በየቀኑ መስቀል የነፍሳችን መዳኛ ነው፣ መስቀል ቤዛችን ነው እያልን በዘወትር ጸሎታችን እንድንጸልየው ያስቀመጠችልን።

ክርስቶስ በዕለተ አርብ በንጹሕ ደሙ መስዋዕትነት ከባሕርይ አባቱ ከአብ ጋር የፈጸመው የማስታረቅ አገልግሎት ከስቅለቱ በፊት ለነበሩ አዳማውያን ብቻ ሳይሆን ከስቅለቱም በኋላ በደሙ ለሚያምኑ ክርስቶሳውያን ሁሉ የተፈጸመ ሕያው የኪዳን ደም ነው።ለዚህ ነው ቅዱስ ጳውሎስ "እግዚአብሔር በክርስቶስ ኢየሱስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበር፤ በደላቸውንም አይቆጥርባቸውም ነበር" ያለው።ቀጥሎም "የማስታረቅንም ቃል በእኛ አኖረ" ይላል።ይህ በእኛ አኖረ የተባለው የማስታረቅ ቃል። የመስቀሉ ቃል ነው። "አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው"ብሎ በማይነገር መቃተት ያሰማው ይህ የመስቀሉ ቃል ለሚጠፋት ሞኝነት ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነው ብሎ ይህ ታላቅ ሐዋርያ በግልጽ ይነግረናል። የቤተክርስቲያን አባቶችም ይህን ምሥጢር መሰረት አድርገው ነው መስቀል ኃይላችን ነው፣መስቀል ቤዛችን ነው፤መስቀል የነፍሳችን መዳኛ ነው ብለው ስለ ዕፀ መስቀሉ ሳይሆን በዕፀ መስቀሉ ላይ ስለ ተፈፀመው ድኅነት በግልጽ ያስቀመጡልን። (2ቆሮ 5፥15፣1ቆሮ 1፥18)

በየዓመቱ የዕፀ መስቀሉን መገኘት በክብር እናስባለን በየዕለቱ ግን የተሰቀለውን ቤዛ በፍቅር እንሰብካለን።የድኅነታችን ዋስትና የተሰቀለው፤ የድኅነታችን ምልክት ደግሞ መስቀሉ ነው።መስቀሉን ባየን ቁጥር የባርነት መጋረጃው ከዓይናችን ላይ ተቀዶ የልጅነት ክብራችን ደመቆ ይታየናል። መስቀሉን ስናይ በአዋጅ የሚቃወመን የትህዛዝ ሕግ በመስቀሉ ተጠርቆ ከመንገድ እንደ ቀረ ትዝ ይለናል።መስቀሉን ስናይ ክርስቶስ ሕዝብና አሕዛብን አይሁድና ግሪክን ሁለታቸውን አዋሕዶ በምድር ሰላምን እንዳመጣ እናያለን።መስቀሉን ስናይ ከአቤል ደም ይልቅ የሚሻለውን የሚናገረውን የኪዳን ደም እናያለን።

የአቤል ደም ከምድር ወደ አርያም ፍረድልኝ እያለ ስለ በቀል የሚጮህ ደም ነበር።የክርስቶስ ደም ግን ከመስቀል ወደ አብ ዙፋን አድንልኝ እያለ ስለ ይቅርታ የሚጮህ የሚሻል የእርቅ ደም ነው።"ወናሁ ደመ መሲህከ ቅዱስ ዘተክህወ በእንቲያየ በቀራንዮ ይኬልህ ህየንቴየ" "ስለ እኔ በቀራንዮ የፈሰሰው የመሲህ ደም ስለ እኔ አሁንም ይጮኻል"ብለው ነው አባቶች የጻፉልን።

"መስቀል ቤዛችን ነው" ፣"መስቀል የነፍሳችን መዳኛ ነው"እያለ የሚጸልይ ክርስቲያን የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ሕያው መታረቂያና መጽደቂያው መሆኑን እየመሰከረ ነው።ክርስቲያን በልቡ አምኖ በአፋ መስክሮ ይጸድቃል።በአንገታችን የምናስረውና በሰውነታችን የምንነቀሰው የመስቀል ምልክት በደሙ ድኛለሁ እያልን የምንመስክርበት ልዩ ምልክታችን ነው።የዳነ ክርስቲያን ደግሞ ይህን ምልክት ተሸክሞ ከአትሮንሱ ሥር ያመሻል እንጂ ከባንኮኒ ጠርዝ አይገኝም ።መስቀሉን በመስቀል ስፍራ እንግለጠው እንጂ ጭፈራ ቤት አንጠልጥለን ክርስቶስን ዳግም አንስቀለው።

ጌታዬና አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ይህ የድኅነታችን አርማ ቅዱስ መስቀል ዘወትር ፍቅርህን ያሳየናል ፤በሞትህ ሞታችንን እንደ ሻርከው ዕለት ዕለት ያስታውሰናል። ውርደታችንን በክብር የቀየርከው በመከራ መስቀልህ ነው። የሚቃወመንን እርግማንም ከመንገድ ጠርቀህ ያስቀረኽው በመከራ መስቀልህ ነው ፤በመስቀልህ በሆነልን ቤዛነት ጽድቅን ያለዋጋ እንዲያው በጸጋ በእምነት ለመቀበላችን ይህ የድኅነት ዓርማ ሕያው ምስክር ነው ፤በመስቀል ላይ ከፍ ብለህ በታየህ ጊዜ ከዓለሙ ነውር ይልቅ ያንተ ንጹህ ደም የአባትህን ዓይን ማርኮታል ዘመኑንም ከዓመተ ፍዳ ወደ ምሕረት ለውጦታል ለቤዛነትህ አንክሮ ይገባል! መከራ መስቀልህ ኃይላችን ነው፣መከራ መስቀልህ ቤዛችን ነው፣መከራ መስቀልህ የነፍሳችን መዳኛ ነው አይሁድ ይክዱታል እኛ ግን እናምነዋለን ያመነውም እኛ በመከራ መስቀልህ እንድናለን ድነናልም ብለን ነው።

ጌታ ሆይ ይህ የተሰቀልክበት መስቀል የድኅነታችን ምስክር ዓርማ ነው። በዕፀ መስቀል ላይ የፈሰሰው ቅዱስ ደምህ መለኮት ተዋህዶታልና ሕያው ነው ፤ ይህ ቅዱስ ደም ከአቤል የተሻለ ደም ነው ስለበቀል ሳይሆን ስለምህረት የሚጮኽ ሕያው መስዋዕት ነው ፤በእምነት ለተቀበሉት ሁሉ በአባትህ ዙፋን ፊት ዛሬም የሚታይላቸው በእግዚአብሔር ዓይን የተወደደ መታረቂያ ነው ።
ኢየሱስ ሆይ በመስቀልህ የጸብን ግድግዳ አፍርሰሀልና ዛሬም ዲያብሎስ በኢትዮጵያውያን መሐል የገነባው የዘረኝነት፣ የመለያየት፣ የክፋት፣ የጸብና የሞት ግድግዳ በመስቀልህ ጉልበት በስምህ ስልጣን የፈረሰ ይሁን።

የመስቀሉ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን።
በጎቹ" ድምፁን ይሰሙታል!

╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
✥┈┈••●◉✞◉●••┈••✥
ከመልአከ ኃይል ቀሲስ ኃይለመለኮት ግርማ ወንድሙ
16/01/2014 ዓ.ም
ከሕይወት ተራራ ላይ መንፈሳዊነት ይብለጥ!
✥┈┈••●◉✞◉●••┈┈✥
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯
3.1K views14:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-20 14:39:19
2.5K views11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-20 14:39:19
ከፎቶ ማህደር
በደሴ ከተማ ለተጠለሉ ተፈናቃዮች ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)ከሰሜን ወሎ ተፈናቅለው በደሴ ከተማ በተለያዩ የመጠለያ ጣቢያዎች ለሚገኙ ተፈናቃዮች ድጋፍ ተደረገ፡፡

መልአከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ በመጠለያ ጣቢያ በመዘዋወር ጉብኝት በማድረግ 500 ፍራሽ እና 300 ኩንታል ዱቄት አከፋፍለዋል፡፡

በዚህም ለድጋፉ ከ2ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ተደርጓል፡፡

መምህር ግርማ÷ የደረሰው ጉዳት አሳዛኝ ነው በማለት ወደ ቀያችሁ ተመልሳችሁ እስክትቋቋሙ ድረስ ድጋፉ ቀጣይነት ይኖረዋል ብለዋል፡፡

አርቲስት ደሳለኝ ኃይሉ በበኩሉ÷ ይህ ሰዓት የምንደጋገፍበትና የምንረዳዳበት ጊዜ ነው ብሏል፡፡

መምህር ግርማም÷ በዚህ ጊዜም ሃላፊነቱን ያልተወጣ ባለሀብት ነገ ኢትዮጵያ የኔ ናት ማለት አይችልም በማለት ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ ተናግሯል፡፡

ከፋና በሰብለ አክሊሉ
2.3K views11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-20 14:39:19
1.9K views11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-20 14:39:19
1.9K views11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ