Get Mystery Box with random crypto!

ባለ ውለታዎቼን ጋሽ ማርቆስ /ማርክ ዙከርበርግ/ እና ስቲቭ፣ ቻድ፣ ጃውድን ጠይቅያቸው መጣሁ! # | ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ባለ ውለታዎቼን ጋሽ ማርቆስ /ማርክ ዙከርበርግ/ እና ስቲቭ፣ ቻድ፣ ጃውድን ጠይቅያቸው መጣሁ!

#_ባለውለታዎቼ_ፌስ_ቡክ_ዩትዩብና_ጎግል!

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ተወዳጆች ሆይ ከማህበራዊ ሚዲያ ተደራሽ፣ ቀላሉና ግንባር ቀደም ከሆኑት ውስጥ ፌስ ቡክና ዩትዮብ ዋነኞቹ ናቸው። ፌስ ቡክን የመሠረተው ማርክ ዙከንበርግ ነው። ዮትዮብን የመሠረቱት ስቲቭ፣ ቻድ እና ጃውጅ ናቸው። እነሱ ደግሞ ለእኔ ብቻ ሳይሆን ለማህበራዊ ተጠቃሚ በሙሉ ባለውለታዎች ናቸው። በለተይ እኔን በግሌ ከምዕመናኑ አስተዋውቀውኛል። ትምህርቶቼን፣ አገልግሎቴን በቀላሉ በተለያዩ ዓለማት ላሉት አዳርሰውልኛል አሁንም እያዳረሱልኝ ነው።

እኔም ውለታቸውን ለማስታወስ በሳንፍራንሲስኮ የሚገኘውን ዋናውን መሥሪያ ቤታቸውን ሄጄ አየሁት። የከበረ ሰላምታዬን አቅርቤ ምስጋናዬን አድርሼ በርቱ ተበራቱ አልኳቸው። ፌስ ቡክ የቀድሞ ሎጎውን ሜታ ብሎ እንደቀየረ ታውቃላችሁ። መሥሪያ ቤቱ ከምነግራችሁ በላይ እጅግ በጣም ሰፊ ነው። ዋና መሥሪያ ቤቱ አሥር ሺ ሠራተኖች አሉት አለኝ ገረመኝ!

በተለይ ዩትዩብ ስሜን ጠይቆኝ፣ በስሜ የምጠቀመውንም ቻናል አሳይቼ በሌላ ጊዜ ስመጣ ከሠራተኞቹ ጋር እንደሚያስተዋውቀኝና አንዳንድ ነገር እንደሚያሳየኝ ቃል ገብቶልኝ፣ ስሜን መዝግቦልኝ በክብር ሸኝቶኛል። መረጃ የሚጎለጉለውን ጎግልንም አይቼው እግረ መንገዴን አመስግኛለሁ።

/ፌስ ቡክ ከሳንፍራንሲስኮ ትንሻ ወጣ ይላል፣ ጎግልና ዩትዩብ እዛው ከተማ ውስጥ ነው ያሉት/

መጋቢት 25-7-2015 ዓ.ም

ካሊፎርኒያ አሜሪካ!