2022-07-29 10:24:37
የዘሩ ምሳሌ
የዘሩ ምሳሌዎች በማቲ 13:3-23
ማር 4: 3-13
ሉቃ 8: 5-13 ተጠቅሰዋል::
በእነዚህ ክፍሎች ውስጥ ዘሪው አንድ አይንት ዘርን በአራት የተለያዩ መሬቶች ላይ እንደዘራ ይናገራል ::
መሬቶቹም
-የመንገድ ዳር መሬት
- ጭንጫ መሬት
- እሾሃማ መሬት እና
- መልካም መሬት ናቸው::
(የማርቆስ ወንጌል ምዕራፍ 4)
2፤ በምሳሌም ብዙ ያስተምራቸው ነበር፥ በትምህርቱም አላቸው። ስሙ።
3-4፤ እነሆ፥ ዘሪ ሊዘራ ወጣ። ሲዘራም አንዳንዱ በመንገድ ዳር ወደቀና ወፎች መጥተው በሉት።
5፤ ሌላውም ብዙ መሬት በሌለበት በጭንጫ ላይ ወደቀና ጥልቅ መሬት ስላልነበረው ወዲያው በቀለ፤
6፤ ፀሐይም ሲወጣ ጠወለገ፥ ሥርም ስላልነበረው ደረቀ።
7፤ ሌላውም በእሾህ መካከል ወደቀ፥ እሾህም ወጣና አነቀው፥ ፍሬም አልሰጠም።
8፤ ሌላውም በመልካም መሬት ላይ ወደቀና ወጥቶ አድጎ ፍሬ ሰጠ፥ አንዱም ሠላሳ አንዱም ስድሳ አንዱም መቶ አፈራ።
. . .
14፤ ዘሪው ቃሉን ይዘራል። ቃልም በተዘራበት በመንገድ ዳር የሆኑት እነዚህ ናቸው፥
15፤ በሰሙት ጊዜም ሰይጣን ወዲያው መጥቶ በልባቸው የተዘራውን ቃል ይወስዳል።
16፤ እንዲሁም በጭንጫ ላይ የተዘሩት እነዚህ ናቸው፥ ቃሉንም ሰምተው ወዲያው በደስታ ይቀበሉታል፥
17፤ ለጊዜውም ነው እንጂ በእነርሱ ሥር የላቸውም፥ ኋላም በቃሉ ምክንያት መከራ ወይም ስደት በሆነ ጊዜ ወዲያው ይሰናከላሉ።
18፤ በእሾህም የተዘሩት ሌሎች ናቸው፥ ቃሉን የሰሙት እነዚህ ናቸው፥
19፤ የዚህም ዓለም አሳብና የባለጠግነት ማታለል የሌላውም ነገር ምኞት ገብተው ቃሉን ያንቃሉ፥ የማያፈራም ይሆናል።
20፤ በመልካምም መሬት የተዘሩት ቃሉን ሰምተው የሚቀበሉት አንዱም ሠላሳ አንዱም ስድሳ አንዱም መቶ ፍሬ የሚያፈሩት እነዚህ ናቸው።
*እነዚህ መሬቶች አንድ አይንት ዘር ቢዘራባቸውም በሚገባ ያፈራው መልካሙ መሬት ብቻ ነበር እዚህ ላይ ማብቀል ብቻ በቂ እንዳልሆነ ማፍራት እንደሚያስፈልግ ያሳየናል ::
ታዲያ አንቺም ልቧሟ እህቴ ይህ መልካሙ የወጣትነት ጊዜሽ
~የልዩ ልዩ የሰይጣን ሃሳብ መተላለፊያ መንገድ ሳይሆን
~በልዩ ልዩ እሾክ በሆነ በዚህ ዓለም ሃሳብ ያስታንቅ
~ጭንጫ ሆኖ በያዝ ለቀቅ እና በለብታ ሂወት ፍሬ ቢስ እንዳይሆን
ፍሬ ለማፍራት የአዝመራው ጊዜ ሳያልፍ እድሜሽ በጨለማው ኃይል ሳይታንቅ እና የቀኑ ክፋት ሳይጫንሽ በጉብዝናሽ ወራት
በመልካሙ ልብሽ ላይ መልካሙን ዘር ዝሪበት::
*ዘሪ ዘርን የሚዘራው በወቅቱ ነው ያለወቅቱ ከዘራ ትርፉ ድካም ነው ማለትም ሰኔ ላይ ካልዘራ ምስከረም ላይ አረም ያጭዳል በውቅቱ ከሆነ አመርቂ እና ያማረ ፈሬ ያፈራል :: ታዲያ አንቺም እህቴ ይህ ያማረው እግዚአብሔርም አለምም የሚፍልገው የወጣትነት ጊዜሽ ሳያልፍ በወቅቱ መልካሙን ዘር ዝሪበት ::
ደግሞም የምታጭጂውን የምታጭጂውን በአንቺ ውሳኔ ሳይሆን በምትዘሪው ዘር አይንት ነው ስለዚህ ምትዘሪውን በጥንቃቄ ምረጪ::
°°የዘሩም ምሳሌ ይህ ነው እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው°°
" ምሳሌው ይህ ነው። ዘሩ የእግዚአብሔር ቃል ነው።"(ሉቃ8-11)
~ለመንገዳችን መብራት
~ለነፍሳችን መድሃኒት
~ ራሳችንን እንድናይ መስታወት
የሆነውን የአምላካችንን ቃል በዘመናችን ላይ እንዝራ እጥፍ ምናፈራ ትውልዶች እንሁን::
ጌታ በፍሬያማ ሂወት የባርከን
Share it
@lebamnegn
@lebamnegn
26 views07:24