Get Mystery Box with random crypto!

Mebruk muhammed @official

የቴሌግራም ቻናል አርማ mebrukmuhammed — Mebruk muhammed @official M
የቴሌግራም ቻናል አርማ mebrukmuhammed — Mebruk muhammed @official
የሰርጥ አድራሻ: @mebrukmuhammed
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 849
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል የተለያዩ ኢስላማዊ ስነ ፅሁፎች - ግጥሞች ወጎች አነቃቂ መልዕክቶች ታሪኮችን ያገኛሉ ለወዳጅ ዘመዶ ሼር ያድርጉ ለአስተያየት እና ለጥቆማ @Congra1
Subscribe to our youtube channel
Watch "AL NESSIM TUBE" on YouTube
https://youtube.com/channel/UCObiz6Wv9GEpjMNi0k8xO6g

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-05-08 12:53:08 ሸቅይ (እድለቢስ) ሰው አራት አይነት ባህሪ አለው

1 የሰራውን ኸይር ስራ ያስታውሳል
2 የሰራውን መጥፎ ስራ ይዘነጋል
3 በዱንያ ጉዳይ የበላዮቹን ያያል በ
4 በዲን ጉዳይ የበታቾቹን ያያል

ሰኢድ (እድለኛ) ሰው ሰው አራት አይነት ባህሪ አለው

1 የሰራውን ኸይር ስራ ይዘነጋል
2 የሰራውን መጥፎ ስራ ያስታውሳል
3 በዱንያ ጉዳይ የበታቾቹን ያያል
4 በዲን ጉዳይ የበላዮቹን ያያል



@mebrukmuhammed
555 views09:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-07 05:48:22 ቁጥር ፍለጋ ተራ ከሚጠብቁ ዜሮዎች ይልቅ ብቻቸውን የቀሩ ነፃ ዜሮዎችን እመርጣለሁ (ፖላንዳዊቷ szymborska)

ገጣሚ ነች በስነፅሁፍ ተክናለች በዘርፉ የኖቤል ሽልማት ካገኙት ተርታም ራሷን አሰልፋለች ብዙ ልዩ አነቃቂ አ.ነገሮችን በመመስረት ዝናን አትርፋለች "ቁጥር ፍለጋ ተራ ከሚጠብቁ ዜሮዎች ብቻውን የቀረ ዜሮ እመርጣለሁ" ከአባባሎቿ አንዱ ነው።

አስር ቁጥር ላይ ያለው ዜሮ ከፊቱ ያለው አንድ ከተነሳ ጥቅም ስለሌለው ለህልውናው ሲል ሁል ግዜም በጥገኝነት የአንድ ቁጥር አጎብዳጅ ነው። ከአንድ ቁጥር በፊት ያለው ዜሮ ግን ሁልግዜም በራሱ ቋሚ ነው ከየትኛውም ቁጥር አይፈልግም ቢያንስ ከኔጌቲቭ ቁጥሮች በልጧል። "ዜሮ እኮ ውጤት ነው ዜሮ አልሰጥህም N.G ወይም incomplete ተብለሀል" ይባል አይደል። ከዚህም ብሶ መቶ ቁጥር ላይ ያለው ዜሮ ከፊቱ ባሉት ዜሮ እና አንድ የተጠጋ ነው። ከባዶም መጠጋት አለ የባሰው አያምጣው መቶ ቁጥር ላይ መሀል ላይ ያለው ዜሮ ደግሞ ከፊቱ ባለው አንድ ተጠግቶ ከኋላው ያለውን ዜሮን አስጠግቷል። ከአንተ የተጠጋህ አለ እና ሙሉ ነህ ማለት አይደለም ባዶም ባዶን ይጠጋልና። ለማንኛውም ህይወትህን በሌላ ሰው ጥገኛ ከመሆን አትርፋት በጥገኝነት ውስጥ ራስን ከመቻል የተሻለ ኑሮ ልትኖር ይችል ይሆናል ነገር ግን አንድ ቀን መጠግያህ የለመድከውን ህይወት የመንጠቅ መብት አለው የተሰጠኸውን ትነሳለህና ሁሌም ራስህን ለመቻል ጥረት አድርግ።

@mebrukmuhammed
527 views02:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-29 06:25:45 <<كثرة حلمك أشكنى عدمك>>
እንዳሉት ሸይኾቹ _ የበደል ዶፉ ባንተ የቁጣ መብረቅ አለመሸፈኑ ይህ ብሶት የወለደው የሀዘን ቅኔ በሸሂዶቹ የደም እንጥብጣቢ በደብዛዛው ተከተበ መሰል። <<የትዕግስትህ ብዛት አለመኖርህን አጠራጠረኝ >> ነበር ያሉት።

ቅንጣት በመኖሩ አልሸከኩም ግን አላህን አምርረው ሲጠይቁ ነው አቅመ_ቢስ'ነታቸውን ሲረዱ የቀዷ እና ቀደር ገፅም ሆኖባቸው እንጂ። ከግሩሙ ቤተ መንግስት ፊትለፊት ያለው ደሳሳ ጎጆዋ በንጉሱ ትዕዛዝ በወታደሮች ሊፈርስ ሲል ለቀናት በመኽሉቅ አቅሟ ዋይ ዋይ ብላ አስቁማ አንድ ቀን ገበያ ጠንታ በትመለስ ጎጆዋ አመድ አንደሆነባት ሴትዬ። እጇንም ከፍ አድርጋ አምለኬ ሆይ እኔ ባለሁበት እንደ መኽሉቅ ዋይ ዋይ ብዬ ዳሴን ጠበቅሁት አንተ ድንገት ባልኖር የት ሄደህ ነው አንተ ያጠበቅክልኝ ብላ ስትለምን ጀሊሉ ዳሷን አልነበረም የመለሰላት ቤተ መንግስቱን ከነሰራዊቱ አወደመው።
ሰይዳችንም በበድር ያለ ሰይፍ ያለፈረስ ጥቂቶችን አልመው ሺዎች ሲጋረጡባቸው የብብት ፀጉራቸው እስኪታይ ድረስ እጃቸውን አንስተው ጌታዬ ዛሬ ካላገዝከን እና ከተሸነፍን ካሁን በኋላ በምድር ላይ ሚገዛህን አታገኝም ነበር ያሉት።
እኛ መጀመርያም ዳሳችንን አላስጠበቅን ቀጥሎም አስጠባቂያችንን አላወሳንም። ተቃውሞ መፈክር ምናምኑ እንዳለ ስንት ያሲን ቀርተናል ስንት ዱዐ ኢስቲግፋር... የእስልምና ድሎች እኮ በመለኮታዊ ሀይል የታጀቡ ነበሩ _ በዚክር ሰለዋት። በስሜታዊ ሳይሆን በስሌታዊ ነጃሳውን በጡሀራ ፍሙን በውሀ እያደረግን።

ለማንኛውም ጁምዐችንን በበኒ በመኽሉቅ አቅም ዋይ ዋይ እንላለን

@mebrukmuhammed
920 views03:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-25 17:05:00 . #ይህንን_ያወቃሉ

ኡሙ አማራህ ረ.ዐ በኡሁድ ጦርነት ረሱልን صلى الله عليه وسلم ከጠላት ለመመከት አስራ ሁለት ቦታ የቆሰለች ሴት ናት ነብያችን ምስክር ሲሰጡ ወደቀኝም ወደግራም አልዞርኩም እሷን ያየሁ ቢሆን እንጂ ብለው ነበር

@mebrukmuhammed
533 views14:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-20 09:33:08 በድር ክፍል አራት
በበድር የወጣቶች ተሳትፎ እና የቁረይሽ ታላላቅ ሰዎች ስለመሞት በጥቂቱ

የሰእድ ቢን አቢወቃስ ረ.0 ወንድም ኡመይር ረ.0 በድር ለመሳተፍ ሲወጣ ረሱል ሰዐወ አስመለሱት። በጣም አዘነ አለቀሰም የሀዘኑን ብርታት ሲያዩ ፈቀዱለት እስኪገደል ተዋጋ። ሰዕድ ረ.0 ረጅሙን የዑመይር ጎራዴ በጣም ረጅም ስለነበር መሬት እንዳይነካ ዘለበቱን ብዙ ቦታ ላይ መቋጠር ነበረብኝ ሲል ወንድሙ ልጅ ከመሆኑ የተነሳ ሰይፉን መሸከም እንዳቃተው ይገልፃል።
ሁለት ወጣቶች ለአብዱ ረህማን ኢብኑ አውፍ አባ ጀህል የታለ ብለው ጠየቁት። ሙዐዝ ኢብኑ አምር ረ.0እና ሙዐዝ ኢብኑ አፍራ ረ.0 ናቸው።ለምን ፈለጋችሁት ሲላቸው የአላህ መልዕከተኛን ይሰድብ አይደል እንገድለዋለን በማለት መለሱ። አቡ ጀህልን በፈረሱ ላይ ሲንጎባለል ተመለከተውና አሳያቸው። አቡጀህል በፈረስ ጀርባ ላይ እነሱ ደግሞ በባዶ እግር ነበሩ። ወደሱ አመሩ አንዱ የፈረሱን እግር በጎራዴው ሲከትፈው አንዱ ደግሞ አቡጀህል ላይ ሰይፉን አሳረፈ። ኢብን መስኡድ በመጨረሻም አንገቱን ቆሮጦ ጣለው። ሙዐዝ ኢብኑ አምር ረ.0 እንደገለፀው አቡ ጀህልን በጎራዴ ስመታው ልጁ ኢክሪማ እጄን በሰይፍ መታኝ። ክንዴ በስጋዬ ተንጠለጠለ። ውጊያ በአንድ እጄ ቀጠልኩ ከዚያም ስቃዩ በአንድ እጄ ሲበረታ እጄን በመሬት አድርጌ በእግሬ በመርገጥ ወደላይ ሰውነቴን ቀና አድርጌ እጄን ከአካሌ አላቀቅኩት። አቡ ጀህል ከሞተ በኋላ ልጁ ኢክሪማ ሬሳውን ወስዶ በክብር ለመቅበር ቢሞክርም አልቻለም። ከሌሎች ከሀዲያን ጋር እንደቆሻሻ ጉድጉዋድ ውስጥ ተጣለ።
ቢላል ረ.0 ሲያሰቃየው የነበረውን የቀድሞ አሳዳሪው ኡመያን በአብዱ ረህማን ኢብኑ አውፍ ረ.0 ተማርኮ አገኘው። ቢላል ተጠግቶ ሊገድለው ሲል አብዱ ረህማን ረ.0 ምርኮኛዬ ነው ሲል መለሰ ቢላልም ረ.0 ጦርነት ሳይቋጭ ምርኮ የለም አለ። ቀጥሎም ሰዎች ሆይ ዛሬ ኡመያ እኔ ሞቼ እንጂ አይተርፍም አለ። ቢላል ረ.0 ቃሉ በተግባር እውን አደረገ ኡመያን በሰይፉ ገደለው
በእለቱ ኡመር ኢብኑ አል ኸጣብ ረ.0
አስ ኢብን ሂሻም የተሰኘውን የገዛ አጎታቸውን በተጠማ ሰይፋቸው የሞትን ፅዋ አቀመሱት።
ሙስአብ ኢብኑ ኡመይር ካፊር ወንድሙ በአንድ አንሳር ተማርኮ ሲመለከት አጥብቀህ እሰረው እናቱ ሀብታም ስለሆነች ከፍላ ታስለቅቀው ይሆናል አለ። ወንድሙም እንዴት በወንድምህ እንዲ ትናገራለህ ሲለው ሙስዐብም ረ.0 ወንድሜ እንተ ሳትሆን የአንሳሩ ሰው ነው አለው።

በድርን በአጭሩ በአራት ክፍሎች ከፍለን እንዲህ ተመልክተናል ከባህር በጭልፋ። አላህ ሱ.ወ የሰሀቦችን የዲን ፍቅር ፣ መስዋትነት፣ ተነሳሽነትን... ያጋባብን።
አ ሚ ን

ምንጭ፦
የተከበረው ቁርአን
ረሂቀል መኽቱም
ፈዳኢሉል አእማል
ሐያቱ ሰሀባ
ተጅሪዱ ሰሪህ
ሪያዱ ሳሊሂን
አል አሀዲሱል ሙንተኸብ

@mebrukmuhammed
740 viewsedited  06:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-18 23:53:11 በድር ክፍል ሶስት
በበድር እለት የተከሰቱ አጃኢቦች
ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት ሰሀቦች ለነብዩ ሰ.0.ወ እኛ ሙሳ ዐ.ሰ ወገኖቹ ሂድ አንተ እና ጌታህ ተዋጉ እንዳሉት አንልህም። ይልቁንስ ከቀኝህም ከግራህም ከፊትህም ከኋላህም ሆነህ እንዋጋለን ብለው ነበር።
ሀኪም ኢብኑ ሂዛም ለኡትባ ይህን ጦር ይዘህ ተመለስ ዘልአለም ምትወደስበት ነገር ነው ብሎት ነበር። ኡትባ በነገሩ ሲስማማ አባ ጀህል ግን ኡትባ እንመለስ ያለው በፍርሀት ነው እንጂ አምኖበት አይደለም አለ። ኡትባ መልሱን ሲሰማ ከእኔ እና ከእሱ ማን እንደፈራ ያያል። አለ አቡ ጀህል የኡትባን ሀሳብ አከሸፈ ስሜት ጥበብን አሸነፈ። ነብዩም ሰዐወ ውጊያው ሊጀመር ሲል በቀይግመል ላይ ኡትባን ሲመለከቱ "ከመሀከላቸው በጎ ሰው ቀይ ግመል ላይ የተቀመጠው ብቻ ነው እሱን ከተከተሉ ቅኑን መንገድ ይይዛሉ " ብለው ነበር።
ነብዩ ሰዐወ የሙስሊሞችን ረድፍ ሲያስተካክሉ እንጨት ይዘው ነበር ለአንድ ሰሀባ "ሰዋድ ሆይ ሰልፍህን አስተካክል" ብለው ወጋ አደረጉት። እሱም "አሳመሙኝ እኮ ብድሬን ልመልስ ይፍቀዱልኝ" አለ። እሳቸውም ሆዳቸውን ገልጠው "ብድርህን መልስ" አሉ እሱም አቀፋቸው እና ሆዳቸውን ሳማቸው።ለምን እንዲ እንዳደረገ ሲጠይቁት "ምናልባትም በዚህ ጦርነት ከሞትኩኝ ከእርሶ ጋር ባለኝ የመጨረሻ የግንኙነት ቅፅበት ቆዳዬ የእርሶን ቆዳ እንዲነካ ፈለግኩኝ" አለ እሳቸውም ዱዐ አደረጉለት።
ኢብሊስ በሱራቃ ቢን ማሊክ ተመስሎ መጥቶ ነበር ከዚያም መላኢኮች ሲወርዱ ደንገጦ ሲሸሽ ሀሪስ ቢን ሀሺም አጥብቆ ሲይዘው ደረቱን መቶት አመለጠ ሙሽሪኮችም "ሱራቃ የት ትሸሻለህ ጎረቤታቹ ነኝ ትለን አልነበር ሲሉት" እናንተ ማታዩትን አያለው አላህንም አፈራለው ቅጣቱም ብርቱ ነው እያለ ሸሽቶ ወደ ባህር ሰመጠ።
የኡካሻ ቢን ሙህሲን ሰይፍ ተሰበረ። ነብዩ ሰዐወ እንጨት ሰጥተውት በዚህ ተዋጋ አሉት ተቀብሎ ሲነቀንቀው ረጅም እና ጠንካራ አብለጭላጭ ሰይፍ ሆነ። በሱም ተዋጋ ሰይፉ "ዓውን" (እገዛ) ተብሎ ይጠራ ነበር። በ "ሁበሩ-ሪዳህ" ጦርነት ሸሂድ እስኪሆን በእያንዳንዱ ጦርነት ተዋግቶበታል።
አል ማዚኒይ እንዲህ ብሏል "አንዱን ካፊር ልመታው እየተከታተልኩት ሳለ ገና ሳልደርስበት ጭንቅላቱ ከአካሉ ተነጥሎ ወደቀ"። በተመሳሳይ ሌላኛው ሰሀባ አንድን ሙሽሪክ እየተከተለ ሳለ ከበላዩ የአለንጋ ድምፅ ሰማ "አይዞህ ቅደም" የሚል ድምፅም ከጆሮው ደረሰ ወደ ኋላ ሲዞር ሰውየው ወድቆ ተመለከተ የአለንጋ ግርፋት ፊቱን ሰንጥቆት፣ አፍንጫውን ሰብሮት፣ አካሉ ወይቦ ተመለከተ። ክስተቱን ለረሱል ሰዐወ ሲነግራቸው "ከሰማይ የመጣ እገዛ ነው" አሉት። ሌሎችም ሰዎች ማንም አጠገባቸው ሳይታይ አንገታቸው ተቆርጦ ይወድቅ ነበር።
አቡ ለሐብ ስለሽንፈቱ የሰማው ከአቡ ሱፍያን ሲሆን ከሰማይና ከምድር መሀከል ቦቃ ፈረስ ጋላቢዎች ነበር የገጠሙን ከፊት ለፊታቸው ማንንም አያስቀሩም ሲልም አከለ። በቦታው የነበረው አቡ ራፊዕ "ወላሂ መላኢኮች ናቸው" አለ አቡ ለሐብ ዘሎ ያዘው ከመሬት ላይ ጣለው። ደካማ ስለነበር መቋቋም አቃተው እላዩ ላይ ተከምሮ ይመታው ጀመር። ኡሙ ፈድል እንጨት አንስታ መታችው ጭንቅላቱ ተፈንክቶ ውርደትን ተከናንቦ ሄደ። ከሳምንት በላይ በህይወት አልቆየም አላህ "አደሰህ" በተሰኘ በሽታ (ቁስል) አስያዘው። በሽታው አረቦች ዘንድ ስለሚፈራ ልጆቹ እንኳ አግልለዉት ብቻውን ተሰቃይቶ ሞተ። ለሶስት ቀናት ሬሳውም አልተቀበረም። የሚደርስባቸውን ነቀፌታ ፍራቻ ጉድጉዋድ ቆፍረው በእንጨት ገፍተው ከተቱት እና ጉድጉዋዱን በድንጋይ እየወረወሩ ሞሉት።
መካዊያን በሽንፈቱ ተዋከቡ ሙስሊሞች እንዳይደሰቱ በሚል ለሞቱ ቤተሰቦቻቸው በቅጡ አላለቀሱም ነበር። አስወድ የተሰኘ በበድር ሶስት ልጆቹን ያጣ አይነስውር በሌሊት የአልቃሽ ድምፅ ሲሰማ አገልጋዩን "ሆዴ ተቃጥሏል ለልጄ አቡ ሀዚማ ላልቅስለት ሂድና መካ ለሙታኖቿ እያለቀሰች እንደሆነ አይተህ ና" አለው አገልጋዩ ቃኝቶ ሲመለስ "አንዲት ሴት ግመሏ ጠፍቷት እያለቀሰች ነው" አለው አስወድ ራሱን መቆጣጠር ተሳነው መካ ለአብራኮቿ ክፋይ ማልቀስ ተስኗት ለአንዲት ግመል መለቀሱ ሆድ ባሰው። ስሜቱንም እያንጎራጎረ ገለፀ።

ይቀጥላል. . .
@mebrukmuhammed
583 viewsedited  20:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-18 10:16:46 በድር ክፍል ሁለት
የውጊያው መጀመር
ሁለቱ ሀይሎች ተፋጠጡ እውነት እና ሀሰት ለመፋለም ወደ ሜዳው ደረሱ። የጦርነቱ የመጀመሪያ ማገዶ አሰድ አል መኽዙሚይ ነበር በአላህ እምላለሁ ከጉድጓዳቸው እጠጣለው ወይ አፈርሰዋለው ወይም እሞታለሁ ብሎ ከረድፉ ወጣ። ሐምዛ ረ.0 ከሙስሊሞች ወጡ ሁለቱ ተፋለሙ አስወድ ተገደለ ክስተቱ ጦርነቱን አጋለው። ከቁረይ ሽ ምርጥ ፈረሰኞች ሶስቱ ወጡ።የአንድ ቤተሰብ አባል የሆኑት የረቢአህ ልጆች ኡትባ እና ሸይባ እንዲሁም የኡትባ ልጅ ወሊድ ነበሩ። የሁለትዮሽ ግጥሚያ ጠየቁ አውስ፣ሚዕወዝ እና አብደላህ ኢብኑ ረዋህ ወጡ "እናንተ ማናቹህ" ሲሉ ጠየቁ "የአንሳር ሰዎች ነን" አሉ "አቻዎቻችንን አስወጡልን ከእናንተ ጋር ጉዳይ የለንም የአጎቶቻቹን ልጅ ነው የምንሻው" አሉ። ረሱል ሰዐወ ሐምዛ፣አሊይ እና ኡበይዳህ ረ.0ንሁማ አንዲወጡ አዘዙ ወጥተው ወደነሱ ሲቀርቡ "እነማን ናቹ" አሉ። ማንነታቸውን ተናገሩ "እናንተስ ከቻዎቻችን ናቹ" አሉ። ሀምዛ ረ.0 እና አሊ ረ.0 ተጋጣሚዎቻቸውን ገደሉ ኡትባ ረ.0 ከተጋጣሚው ተመታቱ አሊይረ.0 እናሀምዛ ረ.0 ተጠግተው ገደሉት። ኡበይዳ ረ.0 እግሩ ተቆረጠ ከበድር ከ4ወይም ከ5 ቀን በኋላ ሞተ። ታዲያ የሁለትዮሽ ግጥሚያው ለቁረይሾች መጥፎ ጅማሬ ሆነ። ምርጥ ፈረሰኞችን አጡ። ቀጣቸው ተቀጣጠለ ሁሉም በአንድነት ሙስሊሞችን አጠቁ ውጊያው ተጋጋመ ፍልሚያው በረታ። ረሡል ሰዐወ ጋቢያቸው እስኪወልቅ ድረስ ዱአቸው በረታ። አላህም የ ከእናንተ ጋር ነኝ መልዕክት አወረደ አንድ ሺህ መለክ እንደሚወርድም ገለፀ። ረሡል ሰዐወ ሸለብ አረጋቸውና ሲነቁ ለአቡ በክር ረ.0 ደስ ይበልህ የአላህ እርዳታ መጥቷል ጅብሪል ይኸውና የፈረሡን ልጓም ይዟል አናቱም አቧራ ለብሷል አሉ። ሙስሊሞች ጠንክረው ተዋጉ በቆራጥነት ተፋለሙ ጣዖታዊያን መፍረክረክ ታየባቸው። ጦርነቱ ወደ ፍፃሜ ተቃረበ። በርካቶች ጣኦታዊያን ጀርባ ሰጥተው ሸሹ ሙስሊሞች ከኋላ እያሳደዱ ማረኳቸው። አቡ ጀህል ግን ፅናቱን አሳየ "ሰዎቻችን መገደላቸው አያስደንግጣቹህ አነዚህን ሰዎች አስረን ነው ምንይዛቸው አትሽሹ በማለት ብቻውን ለማበረታታት ጥረት አደረገ። ብዙም ሳይቆይ በሰይፍ እና በቀስት የተሰራለት አጥር በሙስሊሞች ጥቃት ፈርሶ አቡ ጀህል ፈረስ ላይ ሆኖ ሳለ በሁለት የአንሳር ልጆች የሞትን ፅዋ ቀመሰ። ኢብኑ መስኡድ ጭንቅላቱን በጥሶ ወደ ረሡል ሰዐወ ወሰደው " አላህ ታላቅ ነው ቃል ኪዳኑን ለሞላ ባርያውን ለረዳ ስብብቡን ብቻውን ላሸነፈ አላህ ምስጋና ይድረሰው እንሂድ ሬሳውን አሳየኝ አሉ። አሳያቸው "ይህ የዚህ ኡመት ፊርአውን ነው"አሉ። ጦርነቱ በሙስሊሞች አንፀባራቂ ድል ተቋጨ።
ይቀጥላል. . .
@mebrukmuhammed
412 viewsedited  07:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-17 19:23:52 ሳምንቱን በኢስላም
ወሩ ረመዳን ነው የረመዳን ደግሞ ሁለተኛው ምዕራፍ የመግፊራ ግዜ ላይ እንገኛለን።አኛም አንድ ሺህ አራት መቶ ሰላሳ ዘጠኝ አመታትን ወደኋላ ተመልሰን በዚሁ በራህማ ምዕራፍ የተከናወነውን የታላቁ የበድር ጦርነት ልናስቃኛቹ ወደድን መልካም የንባብ ግዜ።
ክፍል አንድ የበድር ጦርነት መንስኤ

ለአለም እዝነት የተላኩት ዉዱ ነብይ ሙሀመድ ሰዐወ የጥሪያቸው የመጀመርያ ምዕራፍ በመካ ላይ የተደላደለ አልነበረም።ከአንድ ሺህ የሚሻገሩ ቀናቶችን (ሶስት አመት) በድብቅ፣ በሚስጥራዊና ግለሰባዊ ያደረጉትን ዳዕዋ በአላህ ትዕዛዝ ግልፅ ሲያደርጉ በሶፋ ተራራ ላይ አስጠንቃቂ ተደርገው እንደተላኩ ቅርብ ዘመዶቻቸውን ጠርተው በመግለፅ ነበር።
ያኔ የመካ ቁረይሾች ነገሩ ቀስ በቀስ እንቁላል በእግሩ.... የሚለው ስጋት ስለተረጋገጠባቸው በአማኞች ላይ የእሳት በጭድ ላይ ጦርነትን አሀዱ ብለው ጀመሩ። የሰለሙትን ማሳደድ፣ማሰቃየት፣መቅጣት፣ማሰር፣መግረፍ ሌሎችንም ሰላም የሚነሱ ነፃነትን የነፈጉ ኢ- ሰብአዊ ድርጊቶችን መከወን ጀመሩ። ያኔ ለሙስሊሞች የመጀመርያው መፍትሄ ስደት ወደ ሀበሻ ነበር። ቁረይሾች ግን ነገሩ አልጣማቸውም የሙስሊሞች በሀበሻ ሊያገኙት የሚችሉትን ሰላም ሲያስቡ ጉዳዩ እንቅልፍ ነሳቸው። መልዕትተኛ ወደ አቢሲንያ ምድር ልከው ስደተኞቹን ሰሃቦች በወንጀል ፈርጀው በቁጥጥራቸው ለማድረግ ወሰኑ። የሀበሻው ንጉስ ግን በጃዕፈር ረ.0 የሚመራውን የሰላም ስብስብ በአምር ኢብን አል አስ አማካኝነት ከቁረይሽ በተላከው ሙስና ለማለት የሚያስችል የማግባቢያ ስጦታ አና ከአምር ጋር ባላቸው መልካም ግንኙነት ተታሎ የእውነት ስብስብን ከጫንቃው ፈልቅቆ ለቅጥፈት ቡድን አሳልፎ ለመስጠት አልፈቀደም እናም ቁረይሾች ትግላቸውን እዛው መካ ከተማ ላይ አጧጧፉ የማይሳካ ትግል። የያሲር ረ.0 ቤተሰብ ስቃይ፣የሱመያ ረ.ዓ መሰዋት፣አማርን ረ.0 የኩፍር ቃላትን በሀይል ማስነገር የቢላል ረ.0 ሰቆቃ፣ የኸባብ ረ.0በብረት መተኮስ በቁረይሾች ጥሪውን ለማስተጓጐል ከተከወኑ እርምጃዎች አብይ የተባሉት ናቸው። አቡ በክር ረ.0 ሰባት በመስለማቸው ስቃይ ላይ የነበሩ ግለሰቦችን በመግዛ ነፃ አውጥተዋል የሀበሻው ቢላልም ረ.0 ከሰባቱ አንዱ ነው ቀናቶች ነጎዱ ሳምንታት ተፈራረቁ ወራቶች መተካካታቸውን ቀጥለው አመታትም ተቆጠሩ በረሱል ሰ.0.ወ እና በሰሃቦቻቸው ላይ የአረመኔነት በትሮች ማረፋቸውን አላቆሙም መራር ግዜያቶች፣ የሀዘንየ፣ስቃይ፣የጭንቀት፣ የመከራ ዘመንን ለመኖር ተገደዱ በዚህ ሁኔታ ብርሀናማው ጥሪ ግልፅ ከተደረገ አስር አመትን ደፈነ።
በአላህ ፈቃድ ሌላኛው ስደት ተደረገ። የስደቱ መዳረሻ ደግሞ በወቅቱ የስሪብ የምትሰኘው እና የነብዩ ሰ.0.ወ እሷ ዘንድ መግባትን ተከትሎ መዲነተረሱል ወደሚል ስያሜ የተቀየረችው የአውስና የኸዝረጅ ጎሳ መኖርያ የነበረችው ከተማ ነበር ስደቱ እውን ከመሆኑ በፊት ግን መልከመልካሙ እና ተወዳጁ ወጣት ሙስአብ ኢብኑ ኡመይር ረ.0 የየስሪብ መሪዎች የነበሩትን ከባለከራማ ሰሀቦች ረድፍ የነበረው ኡሰይድ ቢን ሁደይር እና ለሞቱ አርሽ የተንቀጠቀጠለት ለቀብር ስርአቱ ሰባ ሺህ መላኢካ የወረደለት ሰዕድ ቢን ዘይድን የእስልምናን ብርሀን እንዲቀላቀሉ መንስኤ ሆኖ ነበር ሌሎች የመዲና ነዋሪዎችንም እስልምናን እንዲቀበሉ አድርጓል። በዚህም ነው ለረሱል ሰዐወ እና ለባልደረቦቻቸው የስሪብ ለስደት ምቹ ከተማ የሆነችው። ይሁን እንጂ ነገሩ ቀላል አልነበረም ሰዎች ወደ የስሪብ ሲሰደዱ የቁረይሽ ጋጠወጦችን ክልከላ በመፍራት አብዛኛው በለሊት ነበር የሚንቀሳቀሱት ኡመር ረ.0 ግን ለሙሽሪኮች የሚያግደኝ ካለ ከተራራው ጀርባ ይጋፈጠኝ ብለው በግልፅ ጉዞአቸውን አውጀው ነበር። እንደ ሱሀይብ አል ሩሚይ ረ.0 ያሉት ደግሞ አሳዳጆቻቸውን በንብረታቸው ተዋውለው መልሰዋል። በአጭሩ ብዙዎቹ ቤታቸውን፣ገንዘባቸውን፣ንብረታቸውን፣ ቤተሰቦቻቸውን ጭምር ወደኋላ ሳይመለከቱ ትተው ለመሻገር ግድ ሆኖባቸዋል። በመካ የሙሀጂሮች ቤት ንብረት በሙሽሪኮች ቅርምት ተወረሰ በመዲና ከአንሳሮች ለመጠጋትም ተገደዱ ይህንን በደል ለማስመለስ አንድ አጋጣሚ ለሙስሊሞች ብቅ አለ። ይህም የቁረይሾችን ወደ ሻም የተጓዘውን ከ50 ሺህ የወርቅ ዲናር የማያንስ ንብረት የተጫኑ አንድ ሺህ ግመሎችን የያዘውን በአቡሱፍያን የሚመራውን ቅፍለት በማገድ እና በመማረክ በቁረይሾች ላይ ብርቱ የኢኮኖሚ ብትር ለማሳረፍ ወርቃማ እድል ነበር። በዙል ኢንሺራህ ዘመቻ በመጀመርያው ሙከራ ቅፍለቱ በማምለጡ የአላህ መልዕክተኛ ሰዐወ ጦልሀ እና ሰእድ የተባሉ ባልደረቦቻቸውን የቅፍለቱን ወሬ እንዲያጣሩ ላኩ። "ሐውራእ" የተባለ ቦታ ሲደርሱ ቅፍለቱን ተመልክተው ወደመዲና በመመለስ ኸበሩን ለነብዩ ሰዐወ አደረሱ። ረሡልም ሰዐወ "የቁረይሾች ቅፍለት አልፏል ብዙ ሀብት የያዘ ነው ስለዚህም አላህ ይቸራቹ ይሆናል" በማለት አወጁ 313 ወይም 314 ሰሀቦች ተዘጋጁ ሰሀቦችን ለዘመቻው አላስስገደዱም። በመካ ያን ግዙፍ ሰራዊት እንደሚጋፈጡ አለማሰባቸው ደግሞ ነገሩን ከሌሎች የተለመዱ የዘወትር ቅኝቶች እኩል አድርገው ለማየት እና ብዙ ሰሀቦች ወደ ቦታው ላለመምራታቸው ምክንያት ነበር። ወሬው ቁረይሾች ጆሮ ደረሰ አቡሱፍያን ለቁረይሾች "ቅፍለታቹን አድኑ የሚለውን" መልዕክት ላከ። ከአንድ ሺህ በላይተዋጊዎች ተዘጋጁ በመሀል አቡ ሱፍያን ቅፍለቱን አስመለጠ። መካዊያን ነገሩን ሲሰሙ ሁለት ቦታ ተከፈሉ ገሚሱ መመለስን ሲመርጡ ከፊሉ ለሙስሊሙ የማያዳግም እምርጃ ለመውሰድ ማይገኝ እድል ነውና ወደ በድር እናምራ አሉ። ሁለተኛው ሀሳብ አመዝኖ 314/313 ሰዎች ከ1300 ሰዎችን የመጋፈጥን አጋጣሚ የፈጠረውን የበድር ጦርነት ለመሳተፍ ጉዞ ወደ በድር ሸለቆ ተጀመረ። ይቀጥላል. . .
@mebrukmuhammed
572 viewsedited  16:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-15 11:45:46 #የረመዳን_ትውስታዎች_4

አንድ በደዊን (ዘላን) ግማሽ አመት ሙሉ(6ወር) ኢልም ሲቀራ ከቆየ በኋላ እስኪ እስከ አሁን ከተማርካቸው ሀዲሶች የሳበህ የቱ ነው ተባለ።
እሱም መለሰ፦
አንደኛ ነብዩ ሰ.0.ወ ማር ይወዳሉ
ሁለተኛ መንገደኛ ሰው (ሙሳፊር) ከመፆሙ አለመፆሙ ይወደዳል
ሶስተኛ ምግብ ቀርቦ ሰላት የለም የሚለው ሀዲስ ነው አለ

የFace book ገፅ
https://www.facebook.com/mebruk.muhamed
540 views08:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-13 11:47:47 #ከረመዳን_ትውስታዎች 3

ሁለት ፆመኛ ሴቶች ከረሱል ሰ.0.ወ ጋር ተገናኙ። ረሱል ሰ.0.ወ ለአንዷ አስታውኪ አሏት በቅፅበት ከሆዷ ደም እዥ ምግል እና ጥሬ ስጋ ወጣ እና ኩባያውን እስከ ግማሽ ሞላው። ለሌላኛዋም አስታውኪ አሏት እሷም እንደ ቀደሟ ከሆዷ ደም እዥ ምግል እና ጥሬ ስጋ ወጣ እና የኩባያውን የቀረውን ግማሽ ሞላው። ከዛም ነብዩ ሰ.0.ወ እነዚህ ሴቶች አላህ ሀላል ያደረገላቸውን ምግብ ከመብላት ታቅበው ፁመው ነበር ነገር ግን ሀራም ያደረገባቸውን የሰው ስጋ በመብላት ፆማቸውን አበላሹት አሉ።

አተርጊብ ወተርሂብ
share

በቴሌ ግራም
@mebrukmuhammed
523 viewsedited  08:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ