Get Mystery Box with random crypto!

መዓዛ ሠናይ

የቴሌግራም ቻናል አርማ meazasenay — መዓዛ ሠናይ
የቴሌግራም ቻናል አርማ meazasenay — መዓዛ ሠናይ
የሰርጥ አድራሻ: @meazasenay
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.95K
የሰርጥ መግለጫ

☞ስለ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖታችን እንወቅ
☞እንረዳ
☞እንማማር
♥♥♥♥♥♥
ለበለጠ መረጃ @Tadi16 ላይ ማንኛውንም ሀሳብ አስተያየት እንቀበላለን፡፡

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-02 05:04:40 ከአክራሪ እስልምና ወደ ክርስትና
#በእውነተኛ_ታሪክ_ላይ_የተመሰረተ
ክፍል 2
#ባለታሪክ_እና_ጸሀፊ
ናሕድ ማሕሙድ ሙቱዋሊ
#ተርጓሚ ዲ/ን ዳንኤል ክብረት

ናታኒም ቲዩብ SUBSCRIBE በማድረግ አገልግሎቱን ያበረታቱ ናታኒም ማለት የእግዚአብሔር ቤት ጠራጊ ታናሽ አገልጋይ ማለት ነውና።






22 views02:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 23:19:34 ከአክራሪ እስልምና ወደ ክርስትና
#በእውነተኛ_ታሪክ_ላይ_የተመሰረተ
ክፍል 2
#ባለታሪክ_እና_ጸሀፊ
ናሕድ ማሕሙድ ሙቱዋሊ
#ተርጓሚ ዲ/ን ዳንኤል ክብረት

ናታኒም ቲዩብ SUBSCRIBE በማድረግ አገልግሎቱን ያበረታቱ ናታኒም ማለት የእግዚአብሔር ቤት ጠራጊ ታናሽ አገልጋይ ማለት ነውና።






37 views20:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 21:58:54 ከአክራሪ እስልምና ወደ ክርስትና
#በእውነተኛ_ታሪክ_ላይ_የተመሰረተ
ክፍል 1
#ባለታሪክ_እና_ጸሀፊ
ናሕድ ማሕሙድ ሙቱዋሊ
#ተርጓሚ ዲ/ን ዳንኤል ክብረት

ናታኒም ቲዩብ SUBSCRIBE በማድረግ አገልግሎቱን ያበረታቱ ናታኒም ማለት የእግዚአብሔር ቤት ጠራጊ ታናሽ አገልጋይ ማለት ነውና።






29 views18:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 20:23:47 ከአክራሪ እስልምና ወደ ክርስትና
#በእውነተኛ_ታሪክ_ላይ_የተመሰረተ
ክፍል 1
#ባለታሪክ_እና_ጸሀፊ
ናሕድ ማሕሙድ ሙቱዋሊ
#ተርጓሚ ዲ/ን ዳንኤል ክብረት

ናታኒም ቲዩብ SUBSCRIBE በማድረግ አገልግሎቱን ያበረታቱ ናታኒም ማለት የእግዚአብሔር ቤት ጠራጊ ታናሽ አገልጋይ ማለት ነውና።






40 views17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 22:40:50 ከአክራሪ እስልምና ወደ ክርስትና
#በእውነተኛ_ታሪክ_ላይ_የተመሰረተ
ክፍል 1
#ባለታሪክ_እና_ጸሀፊ
ናሕድ ማሕሙድ ሙቱዋሊ
#ተርጓሚ ዲ/ን ዳንኤል ክብረት

ናታኒም ቲዩብ SUBSCRIBE በማድረግ አገልግሎቱን ያበረታቱ ናታኒም ማለት የእግዚአብሔር ቤት ጠራጊ ታናሽ አገልጋይ ማለት ነውና።






82 views19:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 06:32:45 ከአክራሪ እስልምና ወደ ክርስትና
#በእውነተኛ_ታሪክ_ላይ_የተመሰረተ
ክፍል 1
#ባለታሪክ_እና_ጸሀፊ
ናሕድ ማሕሙድ ሙቱዋሊ
#ተርጓሚ ዲ/ን ዳንኤል ክብረት

ናታኒም ቲዩብ SUBSCRIBE በማድረግ አገልግሎቱን ያበረታቱ ናታኒም ማለት የእግዚአብሔር ቤት ጠራጊ ታናሽ አገልጋይ ማለት ነውና።






132 views03:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-14 08:51:28 #ሕይወተ_ወራዙት / የወጣቶች ህይወት

(በቀሲስ ህብረት የሺጥላ )

#ክፍል_5

#ከግብረ_አውናን (Masterbation) #እንዴት_መላቀቅ_ይቻላል?

#ሀ. ግብረ አውናን እንደ ማር ጠብታ ነው ። የማር ጠብታ ልብስ ላይ የወደቀ እንደሆነ በፍፁም የሚለቅ አይመስልም ፣ ነገር ግን ትንሽ ለቅለቅ ያደረጉት እንደሆነ ወዲያውኑ ይለቃል። ይህ ክፋ ልማድም እንደማር በቀላሉ ባይሆንም ከልብ በመፀፀት በጠንካራ መንፈስ ከተነሱ ሊያስወግዱት ይቻላል። በመጀመሪያ የሚያስፈልገው ከዚ ነገር መቼም መላቀቅ አልችልም ብሎ ተስፋ አለመቁረጥ ነው ። ከፍተኛ ትግልና ጥረት ይጠይቃል ። ስለዚህ ተስፋ መቁረጥ ፈፅሞ አይገባም

#ለ. ሴጋ ልማድ ነው ። ልማድ ደሞ በሌላ ልማድ ይሸነፋል። ጠንክረህ ከተነሳህ ይህን ተግባር በትዝታ ብቻ የምታስብበት ቀን ሩቅ አይሆንም ። ነገር ግን ከዚህ ልማድ ጋር ለመዋጋት ከመነሳትህ በፊት "ይህን ክፋ ልማድ ምን ያህል ከልቤ ጠልቼዋለው ? " በማለት ራስህን ጠይቅ ። መላልሰህ የምትሰናከለው ሳትፀፀት ወይም ሴጋን መተው ስላልፈለክ ሳይሆን ጣዕሙ በልቡናህ ስላለና ጎጂነቱ ዘልቆ ወደልብህ ስላልገባ ነው ። ስለዚህ ይህን ነገር ከልብህ ልትጠላው ይገባል

#ሐ. ይህን ክፋ ልማድ እንደ እሳት የሚያያይዙት የራስህ ተግባርና በዙሪያህ ያሉ ነገሮች ናቸው ። ከዚህ እኩይ ተግባር መላቀቅ ከፈለክ #ተዐቅቦ ያስፈልግሀል። #ተዐቅቦ ማለት መከልከል መቆጠብ ማለት ነው ። የምትከለከለውም ወደዚህ መጥፎ ሐሳብ ልቡናህን የሚስቡትን ነገሮች ከማየት ፣ ከመስማት፣ ከመንካትና ፣ ከመሳሰሉት ነው ። ስለዚህ የሴቶችን ገላ በፊልምም ፣ በአካልም ቢሆን በምንም መልኩ ከማየት ተቆጠብ። በመዋኛና በመጠመቂያ ቦታዎች ራስህን ጠብቅ የሴት ልጅን መልክና ቅርፅ መርዘህና አተኩረህ አትመልከት ። ስለ ዝሙት የሚያሳስቡ ሥዕሎችን፣ ፅሁፎችን፣ ወሬዎችን ፣ የሴት ገላ የሚያሳዩ የሙዚቃ ክሊፖችን ፣ የወሲብ ፊልሞችን አጥብቀህ ሽሻቸው ።ስራህ ሁሉ አንተው እያራገብክ ለምን ይቃጠላል ? እንዳይሆንብህ

#መ. ዘወትር ልቡናህ የሚጠመድበትን ነገር ፈልገህ አድርግ ። ቦዘኔ አትሁን ትጉህ ሰራተኛ ሁን ።ስራህም አይምሮህን የሚያሰራ ቢዚ የሚያደርግ ይሁን ። ትርፍ ሰአት አይኑርህ ። የሚነበብ ወይም ሌላ የሚሰራ ስራ ፈጥረህ ሥራ

#ሠ. "ሁለት ሁለት አድርጎ ላካቸው " የሚለውን የወንጌል ቃል አስብ ። በዚህ ክፋ ልማድ ተጠምደህ ሳለ ለብቻህ መሆንን አትውደድ ። ቢቻልህ አኗኗርህና መኝታህ ከምታፍረውና ከምታከብረው ሰው ጋር ይሁን ። ይህም ጓደኛህ ወይም ከቤተሰብህ አንዱ ሊሆን ይችላል። በፀሎት ከሚረዱህ መንፈሳውያን መምህራን አባቶች ጋር ጊዜ ማሳለፍን ውደድ

#ረ. እንቅልፍ የያዘህ ስለ መሰለህ ብቻ ወደ መኝታህ አትሂድ ። አንዳንዴ ተኝተህ ውለህ እንቅልፍ ያምርሀልና ። ነገር ግን ሰይጣን ሊፈትንህ ከሆነ በምትነኛበት ጊዜ እንቅልፍ ከአይንህ ይርቃል ። ተከትሎም ፈተናው ይመጣና ወደ ዝሙት ህሊናህ ይሳባል ። ከዛ ሴጋ ትፈፅማለህ። ስለዚህ ከመተኛትህ በፊት በደንብ መድከምህንና ቶሎ ማሸለብ መቻልህን መርምረህ ተኛ

#ሰ. ጸሎት ማድረግንም አትርሳ የሚረሳ ነገር አይደለምና ። ስትተኛም በጀርባህ ወይም በሆድህ አትተኛ ። ከዚህ ይልቅ በጎንህ ለመተኛት ሞክር። አመጋገብህ በልክ ይሁን ፣ ፆምን ፁም ፣ ቅዱሳት መፃህፍትን አንብብ። መዝሙርንም አዳምጥ ዘምር

#ሸ. እንዲህ ያለ ፈተና ሲነሳብህ /አድርግ አድርግ ሲልህ / ከቻልክ ስገድ ።ወይም የሆነ እንቅስቃሴ /ስፖርት / ስራ ። ሽንት መሽናትም ጥሩ መፍትሄ ነው አይምሮህ ሽፍት እንዲያደርግ ያደርገዋል። በየጊዜው ፀበል መጠመቅን ቸል አትበል ። የሴት ገላን ሳታይ

#ቀ. ሰውነትህን አትነካካ ቢበላህ እንኳን አትከከው ። ስታክና ስትነካካው በዛው አድርግ አድርግ ሊልህ ይችላልና ። ንፁህ ሁን ፣ ሻወር ውሰድ ፣ ወክ አድርግ ፣ አንብብ ። ከምንም በላይ አጥብቀህ ፀልይ ። ሁላችንንም እግዚአብሔር ይርዳን ።በቀጣይ የወር አበባን እናያለን

https://t.me/meazasenay
522 views05:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 07:51:24 #ሕይወተ_ወራዙት / የወጣቶች ሕይወት

(በቀሲስ ሕብረት የሺጥላ)

#ክፍል_4

#ግብረ_አውናን(Masterbation)#ተገቢ_ነውን_?

#ግብአውናን የተባለበት ምክንያት አውናን የተባለው ሰው ከሚስቱ ጋር ግንኙነት እየፈፀመ ሳለ ዘሩን ከማህፀን ውጪ ያፈሰው ስለነበር ነው ። ግብረ አውናን/Masterbation (ሴጋ) በመፅሐፍ ቅዱስ ስንመዝነው ተገቢ ነገር አለመሆኑን እንረዳለን ። አንድ ገበሬ ለዘር የሚያስቀረው ዘር ራሱ ከሚመገበው እንኳን የተሻለውን ምርጥ ዘር ነው ። ስለሆነም ከዘር ወቅት በፊት ተጠንቅቆ በጎተራ ያስቀምጠዋል። በዘር ወቅት ደሞ አውጥቶ በመልካም ማሳ ላይ ይዘራዋል እንጂ ያለ ቦታው አይበትነውም ። እንደዚሁም የሰው ዘር ከእህል ዘር ይከብራልና በመልካም ጎተራ ማለትም በሰውነት ተጠብቆ መቆየት አለበት ። ከጋብቻ ቡሃላ ባልና ሚስት ሩካቤ ሲፈፅሙ ደግሞ በመልካምዋ ማሳ በሚስት ማኀፀን መዝራት እንጂ ሆን ብሎ እራስን በራስ በማርካት በየቦታው ማፍሰስ ተገቢ አይደለም ። እራስን በራስ ማርካት /ሴጋ መፈፀም ተገቢ አለመሆኑን የሚያስረዱ በልዩ ልዩ አገባብ የተጠቀሱ ጥቅሶች አሉ

"እንግዲህ በምድር ያሉትን ብልቶቻችሁን ግደሉ እነዚህም ዝሙትና ርኩሰት ፍትወትም ክፋ ምኞትም ፣ ጣዖትን ማምለክ የሆነ መጎምዠት ነው " (ቆላ 3:5) እዚህ ላይ "ብልቶቻችሁን ግደሉ" ሲል ቆርጣችሁ ጣሉ ማለት ሳይሆን አትቀስቅሱ ማለት ነው ። "ደንዝዘውም በመመኘት ርኩሰትን ሁሉ ለማድረግ ራሳቸውን ወደ ሴሰኝነት አሳልፈው ሰጡ " (ኤፌ 4:19) ይህ ጥቅስ ለግብረ አውናንም ሊጠቀስ ይችላል። ምክንያቱም ሴጋ ዝሙትንና ርኩሰትን የመመኘት ዝንባሌ ዋና መገለጫ ነውና ። ሐዋርያው ጳውሎስ በፍትወት ለተቃጠሉ መፍትሄ ሲሰጥ " በምኞት ከመቃጠል መጋባት ይሻላልና ፤ ራሳቸውን መግዛት ባይችሉ ያግቡ " ብሏል ። (1ቆሮ 6:9) ስለዚህ በዝሙት ለሚቃጠሉ መፍትሄው #ማግባት እንጂ #ሴጋ መፈፀም አይደለም። ሐዋርያው ማግባትን እንጂ ግብረአውናንን እንደ መፍትሄ አልመከረምና

ሌላው አምላካችን ሥጋ የፍትወቱን ያህል አግኝቶ እንዲረካ ጋብቻን ሲያሰናዳ ከጋብቻ ጋር አብረው የሚሄዱትን ኃላፊነቶች ከመቀበልና ከመሸከም ጋር ነው ። ነገር ግን ሴጋ ምንም አይነት ኃላፊነት ሳይሸከሙ ያንን እርካታ ለማግኘት እንደ መሞከር ይቆጠራል ።የምኞት ቃጠሎን ዘርን በማፍሰስ ለማብረድ መሞከር ስሕተት ነው ። ምክንያቱም 1 ችግር ሲያጋጥም ተቋቁሞ በማለፍ ፈንታ በተሳሳተ ጎዳና በመጓዝ ችግሩን ለማምለጥ መሞከር ሽንፈትንና ደካማነትን የሚያመለክት በመሆኑ ነው ። በዚ ምክንያት ብዙ ወጣቶች ላለመማራቸውና ለሥራ አጥነታቸው ወይም በሕይወታቸው ለገጠማቸው 1 ችግር ተገቢና ጤናማ መፍትሄ ከመፈለግ ይልቅ ዱርዬነትን ፣ ሌብነትን ፣ ሰካራምነትን፣ ሲጋራ ማጨስንና ጫት መቃምን ፣ በየክለቡ መጨፈርን እንደ አማራጭ ይወስዳሉ

ታዲያ የሽንፈትና የደካማነት ምልክት አይደለምን ? አንዳንድ ሰዎች "1 ሰው ጋብቻ ለመመስረት ዕድሜው ያልደረሰ ወይም ሁኔታዎች ያልፈቀዱለት ከሆነ የጋብቻ ጊዜውን እየተጠባበቀ በዝሙትና በሰዶማዊ ተግባር ከሚሰነካከል ራሱን በራሱ በማርካት ተግባር ቢቆይ አይሻልም ? እስከ ማለት ደርሰው ግብረአውናን/ሴጋ ተገቢ ነገር ለማስመሰል ይጥራሉ። ሁሉም የዝሙት ልዩ ልዩ ገፅታዎች ናቸው ። ሰይጣንም ቢሆን ሐሳቡ እንድንፈፅምለት ከግብረ ሰዶምና ከዝሙት ታንሳለች በማለት ያሳስበናል እንጂ በዚሁ ኃጢአት የተያዙትን ደሞ ያልሰሩት ዝሙትና ግብረ ሰዶም እንዲፈፅሙለት "አንደኛውን ዝሙት ይሻላል ፡ ይህን የመሰለ ኃጢአት እየሰራህ ዝሙት አልሰራሁም ለማለት ነው ? እያለ ተስፋ ለማስቆረጥ እንደሚያምታታቸው መዘንጋት የለብንም።
... ይቀጥላል ...
https://t.me/meazasenay
830 views04:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-24 09:18:42 #የወጣቶች_ሕይወት /ሕይወተ ወራዙት
(በቀሲስ ህብት የሺጥላ)

#ክፍል_3

#ግብረ_አውናን (Masterbation) #ምንድነው ?

እግዚአብሔር ለምህረትና ለመቅሰፍት ያዘጋጃቸው ልዩ ልዩ ግዳጆችን የሚፈፅሙ መላእክት እንዳሉት ሁሉ ሰይጣንም ሰውን በልዩ ልዩ መንገድ እንዲፈትኑ ድርሻ ሰጥቶ ያዘጋጃቸው አጋንንት አሉት ። ከእነርሱም ውስጥ አንዱ #ሰይጣነ_ዝሙት ነው ። ሰይጣነ ዝሙት የሰው ልጆችን የሚፈትንበት መንገድ የተለያየ ነው ። እንደውም አንዳንዶቹ ፈተናዎቹ የዝሙት አይመስሉም

#ፆር_የለመዱ (የሰይጣንን የፈተና ስልት በደንብ ለይተው ያወቁ ) አበው ቅዱሳን ግን ሽንገላ የሞላበትን የሰይጣንን ፈተና አሸንክላ ምን እንደሚመስል መጪ ትውልድ እንዲያውቀው በሕይወታቸው ያዪትንና መንፈስ ቅዱስ ያቀበላቸውን ፅፈው አስቀምጠዋል ። ለምሳሌ ሰይጣነ ዝሙት የሰውን ልጅ ወደ ዝሙት ተግባር ከሚስብባቸው መንገዶች አንዱና ዋነኛው ገሢሥ ነው ። #ገሢሥ ማለት ማሻሸት፣ መነካካት ፣ መዳበስ ማለት ነው ። ነብዩ ሕዝቅኤል "ግልሙትናቸውንም አፍስሰውባት ነበር " (ሕዝ 23:3) በማለት እንደተናገረው ለዘር የደረሱ ወንዶች ከሴቶች ጋር ሲላፋና ሲዳሩ ሩካቤ ሳይፈፅሙ ዘራቸው የሚፈስበት ጊዜ አለ ። ይህን ድርጊት እንደ ተድላ በመቁጠር ብዙ ወጣቶች ሆን ብለው ያደርጉታል

በቅዱስ መፅሐፍ "የድንግልናዋንም ጡቶች ዳብሰው ነበር " እንደተባለው ቦታ ሳይመርጡና ሰው ሳይለዩ የሴት ልጅን ገላ በመዳበስ "ግልሙትናን ማፍሰስ " ያሳፍራል ። ይህ መጥፎ ልማድ የተጠናወታቸው ሰዎች ግርግርና በሰው ብዛት የተጨናነቀ ስፍራ የሴቶችን ገላ እንደ ሐሳባቸው ለመነካካት ምቹ ሁኔታን ይፈጥርላቸዋል። ከነዚህ ውስጥ አንዳንዶቹ ሰው ስራቸውን አይቶ እንዳይነቅፋቸው የተለያዪ ዘዴዎችን ይፈጥራሉ። ለምሳሌ አንዳንዶቹ ምንም ሳያውቁና በእንቅልፍ ልባቸው ያደረጉት ለማስመሰል እንደ ተኛ ሰው እየተገላበጡና እያንኮራፋ በልዩ አጋጣሚ አጠገባቸው የተኛችውን ሴት ገላ ሲዳብሱ ያድራሉ

ይህ ድርጊት ያለ ሩካቤ የወንድ ዘር ከሚፈስባቸው መንገዶች መካከል አንዱ ነው ። ሌሎች ደግሞ በአድካሚ የጉዞ ወቅት ደጋፊ ፣ በሕመም ጊዜ ደግሞ አስታማሚ ... እየመሰሉ ከወሊድ ጋር ተዛምዶ ያላቸውን አካላት ለመደባበስ የሚሞክሩ ናቸው ። አንዳንዶች ደሞ እነርሱ ፈፅሞ ለመንካት እንዳላሰቡ ነገር ግን የተፈጠረው ሁኔታ እንዲጋፋ ወይም እንዲነካኩ እንዳደረጋቸው ለማስመሰል ይሞክራሉ ። በብዛት እንደዚ የሚያደርጉት ሕዝባዊ ስብሰባዎች በሚደረግባቸው እለታትና መጨናነቅ በሚኖርባቸው ስፍራዎች ነው ። ለምሳሌ እንደ ጥምቀት ፣ መስቀል ፣ ኤግዚብሽኖች ፣ የሞሉ ሚኒባሶች ሀይገሮች ባሶችና ባቡሮች መጥቀስ ይቻላል

ሌሎች ደግሞ ውጫዊ ይዘታቸው ሲታይ በዚህ ዓይነት ዘርን በማፍሰስ የመርካት ተግባር የማይጠረጠሩ አይነት ናቸው ። ለምሳሌ እድሜያቸው በጣም የገፋ ፣ በአስተሳሰብ የበሰሉ ፣ በአለባበስና በምጣኔ ሀብት የተከበሩ የሚመስሉ ወይም አስተማሪ የሆነ መንፈሳዊ አቋምና መልካም ስም የያዙ ናቸው ። እንደዚ ያሉት ሰዎች የሌሎችን ህዋሳት ለመነካካት የሚያደርጉት ጥረት "ይህን አስበው አይደለም " እየተባለ ብዙ ጊዜ በበጎ ይተረጎምላቸዋል

ሌላው ዝንባሌያቸው ደግሞ ታዳጊ ህፃናትን ማባለግ ነው ። በቅጡ ጡት ያላጎጠጎጡ ሕፃናትም እንኳን የእነዚህ ሰዎች የጥቃት ሰለባዎች ናቸው ። ህፃናቱ እነዚህ ሰዎች ምን እያደረጉ እንደሆነ አያስተውሉም ፣ አያውቁም ፣ ቢያውቁም አይቃወሟቸውም አይከሷቸውም ። ወይም በትንሽ ነገር ሊባበሉና ሊታለሉ ይችላሉ ።ሕፃናቱን ያጫወቱና ያሳሳቁ በመምሰል ሲታገሉና ሲላፋ በፍትወት እየተቃጠሉ ልብሳቸውን በዘር ጭቃ የሚለውሱትን ወንዶች ቁጥር ቤት ይቁጠረው

... ይቀጥላል
https://t.me/meazasenay
667 views06:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-23 09:00:43 #የወጣቶች_ሕይወት (ሕይወተ ወራዙት)

(በቀሲስ ሕብረት የሺጥላ)
#ክፍል_2

#ሕልመ_ለሊት_መፍትሄ_አለው ?

ብዙ ሰዎች ተግቶ ለመፀለይ ፣ ለማስቀደስና ለመቁረብ በወሰኑ ጊዜ ሕልመ ለሊት እንቅፋት እየሆነ ይፈተኑበታል። በእርግጥ መብላትና መጠጣት ሳያቆሙ ሙሉ ለሙሉ ከሕልመ ለሊት መለየት አስቸጋሪ ከመሆኑም በላይ የሚቻል ነገር አይደለም ። ስለዚህ መፍትሄዎችን እናያለን

#ሀ በመፅሐፈ መነኮሳት ላይ"በሌሊት በሕልም ከሴት ጋር የተገናኘህ መስሎህ ዘር ቢወርድህ በመዓልት አታስባት " ይላል ። ሕልምህን ደስ እያለህ ብታስባት ግን በተግባር ዝሙትን ወደ መፈፀም ያደርስሃል። ስለዚህ ከሕልመ ለሊት ፈተና ለመዳን አንዱ መፍትሔ ሕልምን በውን ደስ እየተሰኙ መላልሶ አለማሰብ ነው

#ለ ሕልመ ለሊት በምታይበት ጊዜ ከነቃህ ቸል ብለህ ተመልሰህ አትተኛ ። ፈጥነህ ተነሳና ተጣጥበህ ጸሎት አድርስ ። ከተቻለህ ስገድ ባይቻልህ ግን የባሕሪህን ድካም ፈጣሪ ያውቀዋልና ይቅር በለኝ ፣ አድነኝ ፣ እያልህ ወደ እግዚአብሔር ለምን

#ሐ ሌላው ከሕልመ ለሊት ለመዳን ዋነኛው መፍትሔ ውኀ በብዛት አለመጠጣት ነው ። መፅሐፈ መነኮሳትም ይሄን ሲመሰክር " እንደ ውኀ ጥም አካልን የሚያደርቅ ፣ከሕልመ ሌሊትና ከዘር መፍሰስ ፣ በቀን ሐጢአት ማሰብን የሚያጠፋ የለም " ይላል ። አንድ ሰው ምንም በጾም አመጋገቡን ቢቀንስ አብዝቶ ውኃ የሚጠጣ ከሆነ አይጠቀምም። ለምን ቢባል ሰውነቱ ስለሚለመልምና ሰይጣን እርሱን ለማሳት መንገድ ስለሚያገኝ ነው ። ስለዚህ ከሕልመ ሌሊት እፎይ ለማለት ከፈለክ "ውኃን ከልክለህ ሰውነትህን አስጨንቀው " ተብለሀል። ወንጌልም ይህን ሲያጠነክር እንዲህ ይለናል ፦ "ርኩስ መንፈስ ግን ከሰው በወጣ ጊዜ ዕረፍት እየፈለገ ውሃ በሌለበት ቦታ ያልፋል ፤ አያገኝምም ። በዚያን ጊዜ ወደ ወጣሁበት ቤቴ እመለሳለሁ ይላል ፣ ቢመጣም ባዶ ሆኖ ተጠርጎ አጊጦ ያገኘዋል " (ማቴ 12-43) ይህ ጥቅስ ብዙ ትርጉሞች ቢኖሩትም ከያዝነው ሃሳብ ጋር የሚዛመደውን ብቻ እንይ ፡" ርኩስ መንፈስ ግን ከሰው በወጣ ጊዜ ዕረፍት እየፈለገ ውሃ በሌለበት ቦታ ያልፋል ። ማለት ሰይጣን መግቢያ ካገኘው ብሎ ሰውነቱን በረሃብና በጥም ወደሚያስጨንቅ ሰው ይሄዳል ማለት ነው ። ይልቁንም "ውሃ በሌለበት" ማለቱን መዘንጋት የለብንም ።"አያገኝምም "የሚለው ቃል ደሞ ሰይጣን ሰውነቱን በውሃ ጥም (በፆም) በሚያስጨንቅ ሰው ላይ ለማደር አለመቻሉን ያሳያል ።

#መ በሕልመ ለሊት በተደጋጋሚ እንዳትጠቃ ወደ ዝሙት ከሚያመራ ማናቸውም ነገር ሽሽ። በመሸ ጊዜ የምታያቸውን ፊልሞች ፣ ንባቦች ፣ ሌሎችንም ነገሮች በጥንቃቄ መርምረህ ለፍትወት የሚያጋልጡትን ሽሽ።ከዚያ ይልቅ ደጋግ መንፈሳዊ መፅሐፍትን ለማንበብ ትጋ ።

#ሠ ሌላው መፍትሄ ደግሞ ከመንፈሳዊ መምህራንና ከአበው ካህናት ጋር እየተመካከሩ በሚያቀርቡት የመፍትሄ ሀሳብ መጓዝ ነው ። እዚህ ላይ ልንጠነቀቅ የሚገባን የምናማክረው ሰው ምስጢራችንን ለመጠበቅ የታመነና በምንነግረውም ነገር ራሱ ወደ ፈተና ሊገባ የማይችል በሕይወቱ ብዙ ተሞክሮ ያለው መሆን አለበት ። እንዲሁም ጥሩ መፍትሄ አለን ፡ ልፋፈ ፅድቅ እንደግማለን እያሉ ከሚያጭበረብሩ ተኩላ ባህታውያንም መጠንቀቅ
አለብን

https://t.me/meazasenay
525 views06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ