Get Mystery Box with random crypto!

Mekdela Amba University Registrar and Alumni Directorate Office

የቴሌግራም ቻናል አርማ maureg1 — Mekdela Amba University Registrar and Alumni Directorate Office M
የቴሌግራም ቻናል አርማ maureg1 — Mekdela Amba University Registrar and Alumni Directorate Office
የሰርጥ አድራሻ: @maureg1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.63K
የሰርጥ መግለጫ

This channel is the official telegram ch of the registrar of MAU, and its purpose is to provide students, teachers and staff with accurate information such as university admission, registration dates, exam programs, academic calendar etc....

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-04-25 21:58:22 https://t.me/MAUREG1
792 views enbere Girma ⓐⓑⓔⓝⓔⓩⓔⓡ, 18:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-25 09:03:55
795 views enbere Girma ⓐⓑⓔⓝⓔⓩⓔⓡ, 06:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-30 04:16:03
1.2K views enbere Girma ⓐⓑⓔⓝⓔⓩⓔⓡ, 01:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-16 13:07:47 Channel name was changed to «Mekdela Amba University Registrar and Alumni Directorate»
10:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-14 17:49:23
ከፍተኛ ትምህርት መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ።

የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ማለፊያ ነጥብ ፦

#ለመጀመሪያ_ዙር_ተፈታኞች !

በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር

• ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 363 ለሴት 351

• በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 351 ለሴት 339

• ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ 300

• በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብ 380

በመጀመሪያው ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 300

• ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 264፣ ለሴት 254

• በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 254፣ ለሴት 250

• ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች 250

• በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ ነጥብ 280

በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 250

(የ2ኛው ዙር ተፈታኞች የመቁረጫ ነጥብ ሙሉ መረጃ በምስል ተያይዟል?!
1.4K views enbere Girma ⓐⓑⓔⓝⓔⓩⓔⓡ, 14:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-27 17:26:36 የአእምሮ ክፍሎችና ስራዎቻቸው
The 3 Levels of the Mind
አእምሯችን 3 ክፍሎች አሉት።

እነዚህም:-

1. ንቁ (Conscious Mind)

2.ከፊል ንቁ(Subconscious Mind)

3.0ድብቁ (the Unconscious) ናቸው።

1. ንቁ የአእምሮ ክፍል
(Conscious Mind)

በምክንያታዊነተ ላይ ተመስርተን በርካታ በእለት ተእለት ድርጊቶችን የምናከናውነው በዚህኛው የአእምሮ ክፍል ውሳኔ መሰረት ነው።

ወደ እምሯችን የሚመጡ ሀሳቦችን ይመዝናል። ከውጭ የመጣውን መረጃ በውስጣችን ካለው ሀሳብ /እምነት ጋር የሚስማማ ወይም የሚፃረር መሆኑን ያረጋግጣል። የሚስማማ ከሆነ ይቀበላል የሚቃረነውን ያስወግዳል።

ለምሳሌ: ስለራሳችን የምናስበው አምራለሁ ብለን ቢሆንና የሆነ ሰው መጥቶ አታምሪም/አታምርም ቢለን ንቁ የሆነው የአእምሮ ክፍላችን መረጃውን በመመዘን ስለራሳችን ከምናስበው ጋር የማይሄድ መረጃ ስለሆነ ወዲያው ያስወግደዋል።

በአጠቃላይ አስበን፣ ሆን ብለን፣ ፈቅደንና በምክንያት/Logic ላይ ተመስርተን የምናከናውናቸው ድርጊቶች በሙሉ የንቁ የአእምሮ ክፍል ውጤቶች ናቸው።

2. ከፊል ንቁ የአእምሮ ክፍል (Subconscious)

ከእኛ ቁጥጥር ውጭ የሆኑ ነገሮችን የምናደርገው በዚህኛው የአእምሮ ክፍል ነው።

ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች እንደ መተንፈስ፣ የልብ ምትና ቅፅበታዊ ነገሮችን የምናደርገው በዚህ የአእምሮ ክፍል በመታገዝ ነው። በስሜት ተነሳስተን የምናደርጋቸው ነገሮች የSubconscious mind ውጤቶች ናቸው።

ሳናስተውል ወይም ሳናገናዝብ ( በከፊል ንቁ የአእምሮ ክፍል ውሳኔ) ባደረግናቸው ነገሮች ኋላ ላይ የምናፍረውና የምንሸማቀቀው ድርጊቱ በንቁ የአእምሯች ክፍል ሲመዘን ነው። ብዙውን ጊዜ ይኼኛው አይሎ ሲመራ እናገኘዋለን።

3. ድብቁ የአእምሮ ክፍል
(the Unconscious)

ድብቁ የአእምሮ ክፍል ያለፉና የቆዩ ከልጅነት ጀምሮ ያጋጠሙን ነገሮችን አጠራቅሞ በመያዝ አሁን ባለው ማንነታችን ማለትም በባህሪያችን፣ ስሜታችን፣ አስተሳሰባችንና ውሳኔዎቻችን ላይ ተፅእኖ ያሳድራል።

በሰው ላይ የሚታዩ ያልተገመቱና ያልተጠበቁ አሉታዊ ባህሪያትና የስነልቦና ውጥረቶች ከድብቁ የአእምሮ ክፍል የሚመነጬ ናቸው።

@BiniGirmachew
1.3K views enbere Girma ⓐⓑⓔⓝⓔⓩⓔⓡ, 14:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-13 18:46:19 መቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ስራውን ጀመረ!!
መቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተለይም በአማራና በአፋር ክልሎች በተፈጠረው የህወሀት ወረራና ዘረፋ ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መካከል አንዱ በመሆኑ ላለፉት አምስት ወራት ከመደበኛ ስራው ውጭ ሆኖ ቆይቷል፡፡

ይሁን እንጂ ዩኒቨርሲቲው ወራሪውና ዘራፊው ቡድን ከቦታው ላይ ከተወገደበት ሰዓት ጀምሮ ምንም አይነት ጊዜ ሳያጠፋ የ60 ቀናት መልሶ መቋቋሚያ እቅድ አውጥቶ ወደ ተግባር በመግበቱ መደበኛ ስራውን ለመጀመር የሚያስችለው ቁመና ላይ ደርሷል፡፡

በዚህም መሰረት የዩኒቨርሲቲው ቦርድ፣ ማኔጅመንት፣ መምህራንና ሰራተኞች እንዲሁም ድጋፍ የሚያደርጉ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የየድርሻቸውን በውቅቱ በመፈፀማቸው ለተማሪዎቹ ጥሪ በማድረግ ከየካቲት 2-3/2014 ዓ.ም ድረስ ተቀብሏል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ በመምህራን፣ በአስተዳደር ሰራተኞችና በተማሪዎች ላይ የተፈጠረውን የስነ-ልቦና ስብራት የሚጠግኑ የአዕምሮና የስነ-ልቦና ውቅር ለውጥ ስልጠናዎችን በሁለቱም ግቢዎች በማደራጀት ከ4-5/06/2014 ድረስ በቱሉ አውሊያ ዋናው ግቢ እየሰጠ ሲሆን በመካነ ሰላም ግቢ ደግሞ ከ7-8/06/2014 ዓ.ም ድረስ የሚሰጥ ይሆናል፡፡

ይህ ስልጠና በዘርፉ ከፍተኛ ልምድና ተሞክሮ ባላቸው ሙያተኞች የሚሰጥ ሲሆን በመምህራን፣ሰራተኞችና ተማሪዎች ላይ ከፍተኛ የስራ ተነሳሽነትንና ፍላጎትን እንደገና በመቀስቀስ በተሟላ ዝግጁነት መደበኛ ስራቸውን በውጤታማነት ለመፈፀም እንደሚያስችልም የአስተዳደርና ተማሪዎች ጉዳይ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሰዋገኝ አስራት በስልጠና መክፈቻ ንግግራቸው ላይ ገልፀዋል፡፡
1.1K views enbere Girma ⓐⓑⓔⓝⓔⓩⓔⓡ, 15:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-09 18:43:30
ለመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ ከ1ኛ እስከ 4ኛ ዓመት #የኤክስቴንሽን ተማሪዎች ምዝገባ የካቲት 07 እና 08/2013 ዓ.ም መሆኑን እናሳውቃለን ።
1.1K views enbere Girma ⓐⓑⓔⓝⓔⓩⓔⓡ, edited  15:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-09 14:23:02
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በጦርነት ለተጎዳው መቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ የአይነት ድጋፍ አደረገ

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የወሀት የሽብር ቡድን አካባቢውን ወሮ በነበረበት ስዓት ከፍተኛ ጉዳት ለደረሰበት የመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ ቱሉ አውልያ ካምፓስ አጠቃላይ ግምቱ 922520/ዘጠኝ መቶ ሃያ ሁለት ሺህ አምስት መቶ ሃያ /ብር የሚያወጣ የአይነት ድጋፍ አድርጓል፡፡

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ልማት ም/ፕሬዝዳንት ዶክተር ድርሻ ደማሜ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንደተናገሩት ‘’የተደረገው ድጋፍ የጠፋውና የወደመው ሀብት የሁላችንም በመሆኑ በጋራ የመተካት ሃላፊነት ስላለብንና አጋርነትንም ለማጠናከር ያለመ’’ ድጋፍ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ድጋፉን የተረከቡት የመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ማ/አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ዶክተር ካሳሁን አህመድ በበኩላቸው ባደረጉት ንግግር ለተደረገው ድጋፍ ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበው ድጋፉ በፍጥነት ወደ ስራ እንድንገባ የሚያግዝና ተቋማቶቹ መካከል በጋራ ለመስራት የመደጋገፍ ባህልንም የሚያዳብር መሆኑን ገልፀዋል፡፡
@mekdela_amba_university
951 views enbere Girma ⓐⓑⓔⓝⓔⓩⓔⓡ, 11:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ