2022-07-05 14:08:06
#ከጥቂት_አመት_በፊት
"በጣም ተጨንቄ ነበር፣ የሰው ልጅ ወይም የሚያባብል የቅፍ ሙቀት ያስፈልገኝ ነበር...መያዝ እና መታቀፍ የምፈልገው ደህንነት እና ተስፋ እንዲሰማኝ ነበር...
መንፈስ ቅዱስ እረዳቴ፣ እንደሆነ አውቃለሁ ነገር ግን የምንግባባቸው ሰዎችን ሰጥቶናል፣ እና በሰዎች በኩል ያጽናናል...
የዛን ቀን ወደ ቤት እየሄድኩ ባለሁበት ታክሲ ውስጥ አንድ ሰው ገባና አጠገቤ ተቀመጠ፣ ከቲንሽ ደቂቃዎች በኋላ እግሬ እግሩ ላይ አረፈ፣ እንዴት.? ማለት.? ምናምን ብላችሁ ሙሉ መረጃ አጠይቁ. እና ስመለስ ወደ ሀሳቤ እረፍት ተሰማኝ፣ ይህ የማስታገስ እና የማቅለል ስሜት ነበር... ውስጤ የሰብአዊነት ስሜት ስላለ ምንም አይነት ምኞት ወይም ሀሳብ አልነበረም...
ያ የድጋፍ ስሜት የሆነ ሰው እጄን ይዞ ደህና እሆናለሁ ያለውን ያህል..
መጽናኛን የሚገልጽ ንጹሕ የሰውነት ግኑኝነት...
ወረድን አመሰገንኩት ግን አልገባውም እኔ ግን አመሰገንኩት።
በሌላ አጋጣሚ እንደዚሁ አንድ ሰው አጠገቤ ተቀምጦ ሳለ ትከሻዬ ላይ ተኛ ረጅም ጉዞ ነበር... አልገፋሁትም ምክንያቱም እንደደከመው እና እንደጨነቀው ስለገባኝ ፊቱ ላይ ይነበብ ነበር እና ፈቀድኩለት...
አየህ ሁሉም ነገር ከጾታዊ ግኑኝነት ወይም ምኞት አይደለም ሰው ተጨንቆ ደክሞታል...
አንዳንድ ጊዜ እነዚህን ነገሮች ሲያደርጉ፣ ብዙ ነገሮችን በአንተ ላይ እያስተላለፉ አይደለም... ሳያውቁት ተከሻችሁ ላይ መጽናናትን ፈልገው ነው...
በነገራችን ላይ ሴቶችና ልጆችም ትከሻዬ ላይ አርፈውብኛል ስለዚህ ወንድ ብቻ ነው ትከሻዋ ላይ የሚያርፈው እንዳትሉ..
የወንድን ምስል እንደ ምሳሌ የተጠቀምኩት ሁሉም ድርጊት ከፆታዊ ግኑኝነት ጋር ብቻ የተያያዘ እንዳልሆነ እንድትረዱኝ ስለምፈልግ ነው...
ቀለል በሉ...
ህይወት ከባድ አይደለችም እግዚአብሔር ከባድ አይደለም...
ሰዎችን ለመግፋት ብዙ ሃይማኖተኛ አንሁን ምክንያቱም የራስ ልክ ያልሆነ ድርጊት አእምሮ ስለሚረብሽ..በነገራች ላይ ሁላችንም ልክ ያልሆነ ጓን አለን ስለዚህ እንረጋጋ ...
ይህ ሰው ቢያንስ ለተወሰነ ጊዜ መተኛት መቻሉን አመስጋኝ እንደነበር መናገር እችላለሁ ትከሻዬ ላይ ቢሆንም እንኳን...
ሲነቃ ይቅርታ ጠየቀኝ እኔም ምንም ችግር እንደሌለው አረጋገጥኩለት... ሙሉ ለሙሉ ገብቶኛል...
ብዙዎቻችን በጭንቀት፣ በድንጋጤ እና ከአእምሮ ጋር በተያያዙ ችግሮች እየተሰቃየን ነው...በማንኛውም ጊዜ ሁላችንም ከነዚህ ሁሉ እርዳታን እና ምቾት እንፈልጋለን፣ አውቀንም ሆነ ሳናቅ...
ለሰዎች እቅፍ እና የፍቅር ቃላትን እንስጣቸው...
ሰዎች በሚያርፉበት፣ እንደዚሁም በትራንስፖርት ውስጥ እየሄዳችሁ ሰዎችን እቀፍ እያልኩ እንዳልሆነ ያዙልኝ...
በነገራችን ላይ አውቄ አይደለም እግሬ እግሩ ላይ ያረፈው..መኪናው ከምንገዱ ሁኔታ ባየር ላይ እንሄዳለን ብል ማጋነን ይሆንብኝ ይሆን.? እና የሁሉ ሰው ሰውነት በተግባር በራሱ ላይ አልነበረም
ነጥቤ ይህ ነው
ህይወትን ቀለል አድርጋት...
የሰዎችን ግኑኝነት ሁልጊዜ ከፆታ ግንኙነት ጋር አትተርጉም...አንዳንድ ሰዎች ድካምና ጭንቀት ውስጥ ናቸው...እና በዚህ መልኩ ህይወትን ማገልገል የእውነት ይቻላል።
@mastewal_tbeb
351 views KATHRYN KUHLMAN , edited 11:08