ውሎ አድሮም ቢሆን በአማራ ብሔርተኝነት ትግል ሰልፍ ውስጥ ባሉ ተዋናዮች ዘንድ ያለው ልዩነት የመስመር ልዩነት ሆኖ እንዲህ ፍጥጥ ብሎ መውጣቱን ወድጄዋለሁ። ሰው በሚያምንበት መስመር መታገሉን ትግላችን የሚያከብረውና እውቅና የሚሰጠውም ስለሆነ ከዚህ አንፃር ያሉ የአሰላለፍ ግራጫዎች እየጠሩ መሄዳቸው ለሕዝባችንም ጠቀሜታው የጎላ ይሆናል። በትግል መስመራችን ውስጥ ወንድማማችነትን ለሕግ ትርጉም፣ ዳኝነትና ብይን የምናቀርበው አልነበረም፤ አይደለም፤ አይሆንምም። የወንድማማችነት መንፈስና እሴት ላይ ጥያቄ ያለው አካል በአንድ የፖለቲካ ትግል መስመር በተለይም ደግሞ በብሔርተኝነት የትግል መስመር ላይ ሊገኝ ግን አይችልም። በየሰልፋችን እንሁን። ይኸው ነው! 3.6K views05:23