Get Mystery Box with random crypto!

...............

የቴሌግራም ቻናል አርማ mame_graphics — ............... M
የቴሌግራም ቻናል አርማ mame_graphics — ...............
የሰርጥ አድራሻ: @mame_graphics
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 326
የሰርጥ መግለጫ

"አላህ አዋቂም ጥበበኛም ነው"🎨
☞ ኢስላም በራሱ ውበት ነው ፣ ጥበብም ነው።
♢ በሀዲስ ላይ ረሱል ሰ.ዐ.ወ እንዳሰፈሩት:-
 ❤“.. إن الله جميل يحب الجمال ..”♥ ☞
-
-
-
♡"ያ ረብ ለሰጠከኝ ፀጋ ሁሉ አመሰግናለሁ!" ♡
4_ᴀɴʏ pʀᴏɴᴏ & Cᴏᴍᴍᴇɴᴛ { @mamella_bot }
{ 0942506410}

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-04-22 21:58:51 ወርቁን ማን ሰረቀው
ክፍል ዘጠኝ
(ነኢማ ኸድር)

........በጣም ተጎድተሻል እያለች ወደኔ መጣች
ግራ ገባኝ ስለማነው እምታወራው ከሰአታት በፊት ለካ ጤነኛ ነበርኩ ገረመኝ እኛ ሰወች እንዲህ ደካማ መሆናችንን ሳስብ አምላኬን ለመጥራት ተሸማቀኩ ለካ እንዲ ደካማ ነን እንደምንም ለመናገር ልሞክር ስል አፌን ማንቀሳቀስ ተሳነኝ ምግብ ስላልበላሁ ነው መሰለኝ እናቴ እንደነቃሁ ስላወቀች እንደ ምንም እራሷን አረጋግታ ወደ ክፍሉ ገባች ገና አልጋው ላይ ስታየኝ እሪታዋን አቀለጠችው እኔም ድምፄ ባይወጣም እንደተኛሁ በቀኝ በግራ አጣደፈኝ እንደማይነጋ የለምና ነጋ ጠዋት ላይ ሂክማ የምትባል ጎረቤታችን ቁርስ ሰርታ ይዛልኝ መጣች ገና ሳያት ገረመኝ ሴትየዋ ከኛ ቤት ፊት ለፊት እንደሆነች አቃለሁ እሱንም ያወኩት አንድ ቀን ከሰፈር ወጥቼ ታክሲ ስጠብቅ ሸኝታኝ በአይን እንደምታቀኝ ነገረችኝ እንደዛ እያወራን ነው ጎረቤቴ መሆኗን ያወኩት
ገና ስትገባ ሳቄ መጣ አይ ሀበሻ ለካ ለችግር ደራሽ ነው የያዘችውን ዘንቢል እያስቀመጠች "ፈርሁ እንዴት ነሽ? አሁን ለውጥ አለሽ?ሀኪሞቹ ምን አሉሽ?" የጥያቄ መአት አዘነበችብኝ እስቲ ፍረዱ አሁን ለህመምተኛ እንዲ ይጠየቃል ያውም ለንደኔ አይነቷ ሆሆሆሆ

አክስቴ ከአፏ ቅብል አርጋ አልሀምዱ ሊላህ ደና ነች እንደው በጊዜ ታውቆላታል አልሀምዱሊላህ ማለቱ ነው የሚበጀው እያለች ወደውጪ ወጣች
ወዲያው ዶክተሩ በሩን ከፍቶ ገባ አሰላሙ አለይኩም ብሎ ወደኛ መጣ ሂክማ ድምፁን ስትሰማ በቅፅበት ዞር ብላ አየችው መርዋን ብላ ተነሳች ሁለቱም ለረዥም አመት እንዳልተገናኙ ያስታውቃል ሂክማ ከመቀመጫዋ እየተነሳች "ያ አላህ 7 አመት ቡሀላ ማለት አዏ ግን በጣም ተለውጠሀል"እያለች በአግራሞት ታየዋለች ግን ሁለቱም እንደመነፋፈቃቸው አልተጨባበጡም አልተቃቀፉም እሱም በግርምት ከራስ ፀጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ ካገላበጣት ቡሀላ
"ትዳር ተስማምቶሽ የለ እንዴ ሂኩ በአላህ እንዴት እንደናፈቃቹሁኝ አክስቴ እንዴት ናት ? "ሲል ገባኝ
እህህህ የ አክስቱ ልጅ ናት እህህ ትንሽ ካወሩ ቡሃላ"ኦኦ ፈርሁ እንዴት አደርሽ አሁን እየለቀቀሽ ነው ሳናስበው ስለተገናኘን ነው እሺ እንዲህ ቁመን ያወራነው"እያለ ወንበሩ ላይ ተቀመጠ ሂክማ ወደኔ እያየች ጥሩ ጎረቤቴ ናት ተንከባከብልኝ ብላው ፈገግ አለች
ዶክተር መርዋን ወደኔ እያየ እሷ ከረዳቺኝ አለ
"ምን ለማለት ፈልጎ ነው "ማለት አለች ሂክማ ዶክተር መርዋን ከተቀመጠበት እየተነሳ ምግብ እና መጠጥ በደንብ የምትወስድ ከሆነ ነው"እያለ ለመሄድ በሩን ከፈተው እና እንደመመለስ እያለ ኦ ሂክ ስልክሽን ንገሪኝ ስራ በሌለ ጊዜ እንገናኛለን"ብሏት ስልኳን ተቀብሏት ወጣ ሂክማ የሌለ ተንከባከበችኝ ከባሏ ጋር እየተቀያየሩ ሳምንቱ ሙሉ ከ እናቴ ጋር ቆይተው ይሄዳሉ ሰው እንዴት ለማያውቀው ሰው እንደዚህ ይሆናል ወይ ሀበሻ እንደምቀኝነቱማ እኮ ሆዱ ባዶ ነው ከሁሉም ግን የገረመኝ የዶክተር ተብዬው ነው ስራ በሚወጣበት ሰአት ከኔ ጋር

ከ 2 እስከ 3 ሰአት ይቀመጣል እና ዘና አርጎኝ እናቴ ስትመጣ ይሄዳል የሌለ ምርጥ ሰው ነው እርጋታው አወራሩ በቃ ሁሉ ነገሩ ቀልብ ይመስጣል ዶክተር መርዋን አላገባም እንደውም እሱ እኔ ጋር ሆኖ ሂክማ ከመጣች ስለትዳር እያወራች ታሸማቀዋለች እንደውም አንድ ቀን በቁም ነገር ጠየኩት ???
የኔ ሀዋ ገና አልተፈጠረችም ብሎኝ ጥሎኝ ወጣ እንዲህ እንዲህ እያልን ሳምንቱ አልቆ ከሀኪም ቤት እምወጣበት ቀን ደረሰ ሂክማ ከነ ባለቤቷ አክስቴ እና እናቴ ሁነው መተው በነ ሂክማ መኪና ወሰዱኝ አማር ግን ሳምንቱን ሙሉ አልመጣም አልጠየቀኝም ሀጂም ኢነብንም አላየሁዋቸውም ለምን ግን አንዳቸው እንኳን አልመጡም አማር ምን ሆኖ ነው የጥያቄ መአት ጭንቅላቴ ላይ አዘነብኩበት ....
የነ ሀጂ ቤተሰቦች እየገረሙኝ ሳለ 3 ቀን ሞላኝ ህመሜ በደንብ ባይለቀኝም ግን እንቀሳቀሳለው ዛሬ ግን ገና ከጠዋቱ ጭንቅላቴን ወጥሮ ይዞኛል እንደነገሩ የአቅሜን ሰርቼ ፍራሽ ላይ በጎኔ ተኝቼ ቴሌቪዥን እየተመለከትኩኝ ሳለ የጊቢው በር ተንኳኳ እማዬ ከ አክስቴ ጋር ከትንሽ ደቂቃ በፊት ወጥታለች በሩን ለመክፈት ወደ ውጪ ወጣሁ የመግቢያውን በር ጨርሼ በረንዳውን እንዳለፍኩ ጭልም አለብኝ እዛው ቁጭ አልኩኝ በሩ አሁንም እየተንኳኳ ነው እንደምንም በሩን ከፈትኩት ዶክተር መርዋን ነበር
"አሰላሙ አለይኩም ፈርሁ ደና ነሽ በአላህ አልተቀየምሺኝምማ" እያለ ፈገገ አለ እኔ ልውደቅ ልቁም እያልኩ ከራሴ ጋር እየተሟገትኩ ነው ሳላስበው የ መርዋንን ክንድ ጥብቅ አድርጌ ያዝኩት "ምነው ፈርሁ አሞሻል እንዴ "እያለኝ ደገፈኝ መቆም ስላልቻልኩ "ወደቤት እንግባ" ብዬው ደገፈኝ እና ወደቤት ልንገባ እግሬን ሳነሳ ተዝለፍልፌ እጁ ላይ ቀረሁ ከትንሽ ደቂቃ ቡሀላ አማር በመኪና አደጋ እንዳረፈ ተነገረኝ የሆነ የማቀው ሰው ይመስለኛል እነ አማር ቤት ወሰዶኝ ጊቢው በሰው ታፍኗል ሀጂ እንባቸው ብቻ ይፈሳል የአማር ጀናዛ
(አስክሬን)ተሸክመው ሲያወጡት ኢነብ ወንድሜ ብላ ስትጮህ አይኔን ከፈትኩና "አሚሚሚ"ብዬ ጮህኩኝ እናቴ አክስቴ መርዋን እና ሂክማ ዙርያዬን ከበውኛል ሁሉም ተጨንቀዋል መርዋን ወደኔ እየተጠጋ "ምንድነው ፈርሁ ማነው" እያለ በ አትኩሮት ያየኛል በሰለለ ድምፅ "እማዬ አማር ሞተ" አልኳት ከተቀመጠችበት ብድግ እያለች "የምን ሞት ነው ጠዋት መቶ እኔ አንተ አትገባም ብዬ የመለስኩት" እያለች አፈጠጠችብኝ

መርዋን በአትኩሮት እየተመለከተኝ ድምፁን ቀነስ አርጎ ጎደኛሽ ነው" አለኝ እንዴት እንዲ ሊል ቻለ? ጭንቅላቴን ከቀኝ ወደግራ ነቅነቅ አረኩት መርዋን ከ ዶክተርነት በዘለለ የ ስነ ልቦና ሀኪም ና አማካሪ ነው ይህንንም ያወኩት ሀኪም ቤት በነበርኩበት ወቅት ነግሮኝ ስለነበረ ነው እነ አክስቴን ወደ ስራቸው እንዲመለሱ አሳምኖ አጠገቤ መቶ ያወራኝ ጀመር "አማር ምንም አልሆነም ስለሱ ስለተጨነቅሽ ነው አንዳንዴ አይምሮአችን ስለ አንድ ሰው ከመጠን በላይ ሲያስብ እራሳችንን እንስታለን ከዛ የምንነቃው ስለዛ ሰው አይምሮአችን መልክት ሲልክ ነው እያለ ብዙ ተነተነልኝና በመሀል ዝም አለ ወንድን በሙሉ አይኔ ከ አንዴ በላይ ማየት አልወድም ሀይማኖተኛ ምናምን ሆኜ ሳይሆን በቃ ደስስ አይለኝም መርዋን ከፊትለፊቴ ተቀምጧል ሁለታችንም ዝም ብለናል ዝምታውን ለመስበር ሁለታችንም እኩል "ግን" አልን መገጣጠማችን ገርሞን ሳቅን " ግን ምን ልትይኝ ነበር " አለኝ እየፈገገ " አንተ ምን ልትል ነበር " አልኩት ጥያቄውን በ ጥያቄ ስመልስ "አንቺ ንገሪኝ" ቅድሚያ ለ ሴት" እያለለ አሁንም ፈገገ " ታካሚዋን በ ጥያቄ መወጠር ክልክል ነው" ብዬው ከት ብዬ ሳኩኝ ነገረ ስራዬ ስለገረመው እየተያየን ሳቅን መርዋን በቅፅበት ሳቁን አቁሞ "ግን እስከዛሬ ለምን አላገባሽም ? ማለቴ ቆንጆ ነሽ ስርአት አለሽ ታዲያ እንዴት ?" ብሎኝ ፈገግ አለ ጥያቄው ቢያስደነግጠኝም ፈገግ እያልኩ "የኔ አዳም ገና አልተረገዘም" ብዬው ሙድ ያዝኩበት እንደ ድንገት በሩ ተንኳኳ አክስቴ በሩን ልትከፍት ወጣች " ግቡ "ስትል ይሰማል ማን ነው?
የሳሎኑ በር እየተንኳኳ.....

ይቀጥላል.......

➥ሼር እንዳይረሱ
JOIN ⇒ @mame_graphics
293 viewsΜαμε, 18:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-07 21:28:12 رمضان كريم
278 viewsΜαμε, 18:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-15 17:36:59
#MidrocInvestement: የድርጅታችን ባለቤት የሆኑት ሸህ አላሙዲን በወሰኑት መሰረት ከደንበኞቻችን ጥብቅ ትስስር ለመፍጠር የዘመናችን ተመራጭ የመገናኛ ዘዴ የሆነውን የቴሌግራም ገፅ ከፍተናል፡፡ በመሆኑም ገፃችን ሼር አድርገው ተደራሽ ላደረጉ ደምበኞች ጥሩ ማበረታቸ የሚሆን የመኪና ስጦታ አዘጋጅተናል ሱዙኪ ኤርቲጋ 2021 ሞዴል እንሸልሞታለን ፡፡ በመሆኑም ሊንኩን ተጭነው ከገቡ በሗላ ይህን ፅሁፍ ለ60 ጓደኛዎ ሼር ያድርጉ የመሸለም እድሎ የሰፋ ነው ይህን የማይገኝ አጋጣሚ በከንቱ እንዳያሳልፉ አሁኑኑ ፎርዋርድ ያድርጉ ፡፡ ይህን ሊንክ ይጫኑ : @midrocinvestment
301 viewsΜαμε, 14:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-10 08:36:21 ደስ የሚል ታሪክ ነው!!!

ሁለት ሰዎች በአንድ ሆስፒታል ክፍል ውስጥ አልጋ ይዘው ተኝተዋል! ... ሁለቱም በጠና ታመው በአምላክ እጅ ተይዘዋል። አንደኛው ሳንባው የቋጠረውን ውሀ ለማድረቅ ሲባል
ለሰአታት ያህል አልጋው ላይ ቁጭ እንዲል ይደረጋል ... አልጋው የሚገኘው በክፍሉ ብቸኛ ከሆነው መስኮት አጠገብ ነው። ሌላኛው ህመምተኛ ደግሞ በተቃራኒው ለሰአታት
በጀርባው እንዲተኛ ይደረጋል።
እነዚህ ህሙማን በቆይታቸው ብዙ ተጨዋውተዋል። ስለ ቤተሰቦቻቸው፣ ስለ ኑሯቸው፣
በወታደር ቤት ስለሰጡት አገልግሎት፣ የእረፍት ጊዜያቸውን የት እንደሚያሳልፉ... ወዘተ
አውርተዋል።
ከመስኮት አጠገብ ያለው ህመምተኛ ቁጭ በሚልበት ሰአት ወደ ውጭ እየተመለከተ
ሁሉን ነገር በጀርባ ለተኛው ሰው ይገልጽለታል። ".....በሚያማምሩ ዛፎች የተከበበ ሀይቅ ይታየኛል ... በሀይቁ ላይ ዳኪዬዎች ይዋኛሉ...... ህጻናት ደግሞ ከወረቀት የሰሩትን መርከቦች በሀይቁ ዳርቻ በማስቀመጥ ይጫወታሉ... ፍቅረኛሞች በአንድ
እጆቻቸው አበባ በሌላው ደግሞ ተቃቅፈው ሀይቁን ይዞራሉ .. ከሀይቁ ባሻገር ውብ
የሆነ ከተማ ይታየኛል .... ህፃናቶችም በደስታ ይቦርቃሉ " በማለት ዘወትር የሚያየውን ሁሉ በሚያምር አገላለፅ ይተርክለታል! ... በዚህ
አይነት ሁኔታ ሳምንታት አለፉ።
አንድ ማለዳ ነርስዋ ገላቸውን ልታጥብ ውሀ ይዛ መጣች። ከመስኮት አጠገብ ያለው
በሽተኛ ግን በህይወት አልነበረም። በጣም ደነገጠች። ጓደኛውም እንዲሁ አዘነ።
ነርስዋ አስከሬኑን በቶሎ እንዲያነሱ ሰዎች ሌሎች ነርሶችን ጠርታ አዘዘቻቸቸው! ... ያ ብቻውን የቀረው በሽተኛ አልጋውን ከመስኮቱ አጠገብ ሊወስዱለት ይችሉ እንደሆነ ጠየቀ። ወሰዱለት። በመስኮት ለማየት በጣም ቸኩሏል። ቀና ብሎ ወደ ውጭ ተመለከተ። ከመስኮቱ ባሻገር ያለው ጥቁር ቀለም የተቀባ ግድግዳ ብቻ ነው። ደነገጠ!!!
"ምን ሆንክ?" አለቸው ነርሰዋ። "ሰዉዬው ብዙ አስደሳች ነገሮችን በዚህ መስኮት
አሻግሮ ይመለከት ነበር" አላት። "ኧረ ሰዉዬው ማየት የማይችል አይነስውር ነበር
አለችው።"
ልብ የሚነካ ነገር.... ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ። ለካስ እሱን ለማስደሰትና የመኖር ተስፋ
ለመስጠት ነበር ያን ሁሉ ነገር ፈጥሮ የሚያወራው።

አስተማሪ ይሆን ዘንድ ለወዳጆ ያጋሩ
327 viewsᴀʙᴅᴜssᴇʟᴀᴍ ᴀʟ-ɢʜᴀᴢɪ, 05:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-09 17:52:52 Promise day
ዛሬ የpromise ቀን ነው እና ከጓደኞችክ/ሽ መሀል ለምቶዳቸው መርጠክ/ሽ ለ 18ቱ ብቻ ላክ/ኪ

ቃል እገባለው አንተ/ቺ
በህይወቴ ልርሳቸው ከማልችላቸው ጓደኞቼ መሀል አንዱ ነክ/ሽ ዛሬ የ promise ቀን ነው ይሄንን መልክት በህይወታቹ ልትርሷቸው ለማትችሏቸው ጓደኞች ይላኩላቸው

እኔም ከሆንኩ ላክልኝ/ላኪልኝ
@mame_graphics
385 viewsΜαμε, 14:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-20 11:36:06 ጥሎ ረጅም ገመድ ወደ ላይ ተንጠልጥሎ አንድ የላስቲክ ከረጢት ውስጥ ውሀ ሚመስል ነገር ወደ ቀጭኑ የገመድ ቱቦ እየወረደ እጄ ላይ ባለው መርፌ ውስጥ ይገባል ምን ሆኜ "ነው? የትስ ነው ያለሁት?"እያልኩ እራሴን ጠየኩኝ እጄን ሳንቀሳቅስ አክስቴ "ነቃች ነርስ ነርስ እያለች ተጣራች" ወዲያው 2 ነጭ ለባሾች መጡ አንዷ ሴት ናት ነርስ ነች መሰለኝ ሁለተኛውን ዶክተር እያለች ነው ምታዋራው ሁኔታዬን ካዩ ብሀላ አክስቴን ወደ ቢሮ እንድትመጣ ነግረዋት ወጡ እናቴ አሁንም ታለቅሳለች ሊያረጋጓት አልቻሉም አክስቴ ከግማሽ ሰአት ቡኃላ መጣችና እያየቺኝ ማልቀስ ጀመረች ምንድነው ዛሬ ሰው ሁሉ ሚነፋረቀው?ማን ሞቶ ነው እያልኩ እራሴን በራሴ ጠየኩኝ አክስቴ ወደኔ እየመጣች ይሄን ሳምንት እዚ ነሽ በጣም ተጎድተሻል እያለች......

ይቀጥላል...

➥ሼር እንዳይረሱ

JOIN ⇒ @mame_graphics
•┈┈┈┈•✿❥❥✿•┈┈┈┈•
490 viewsΜαμε, 08:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-20 11:36:06 ወርቁን ማን ሰረቀው
ክፍል ስምንት
(ነኢማ ኸድር)

........በሩን ለመክፈት የያዝኩትን ቦርሳ ፍራሽ ላይ ወርውሬ በሩን ልከፍት ወደ ጊቢው አቀናው "ግን ማን ይሁን? በዚ ሰአት እኛ ቤት ማን ሊመጣ ይችላል "ብዬ በሩ ጋር እንደደረስኩ የበሩን መቀርቀሪያ ከፍቼ በሩን ወደኔ ሳብኩት በመጀመሪያ ሀጂ ከዛ አማር በመቀጠል ፈርሂን ከሷ ቀጠል አርጎ ወጣቱ ልጅ እንደጉድ ተከታትለው ገቡ በጣም ተገርሜ በሩን እንደ ከፈትኩት ቆሜ ቀርቻለው እንደ ድንገት የእናቴ ድምፅ ከገባሁበት አግራሞት አነቃኝ "መጣው መጣው"ብያት እየሮጥኩ ወደቤት ገባው ለጦር ሜዳ እንደ ተዘጋጀ ወታደር በመደዳ ተደርድረዋል እናቴ ከነሱ ፊት ለፊት ከመግቢያው ተቀምጣለች ሀጂ እኔ መግባቴን እንዳወቁ እናቴ አጠገብ እንድቀመጥ በ እጃቸው ምልክት ሰጡኝ ወዲያው እናቴ አጠገብ ተቀመጥኩ ኢነብ እየተቁለጨለጨች በዐይኗ "ምንድነው?"አለችኝ እኔም እንደርሷ ግራ ስለገባኝ በከንፈሬ እና በግንባሬ ምልክት እያሳየኀት "እኔንጃ" አልኳት ሀጂ ቀና ብለው እያዩኝ ንግግራቸውን ጀመሩ "ፈርሁ እኔ ኢነብ እንድትሰሪ ካመጣችሽ ቀን ጀምሮ እንደ ልጄ ነበር የማይሽ ግድ የለም ሸይጣን(ሰይጣን) አሳስቶሽም ከሆነ ግድ የለም መፍትሄ ይበጅለታል ሀቁን (እውነቱን) ንገሪን እያሉ አይን አይኔን ያዩኛል የሀጂ ንግግር ሁሉንም አስደነገጠ አማር ይበልጥ ንድድ ብሏል ሀጂ ንግግራቸውን ለመቀጠል "ደግሞ"ሲሉ አማር ከተቀመጠበት ብድግ ብሎ"መጠየቅ ካለባትም ለምን እሷ ብቻ እኔም አብርያት አልነበርኩ እኔም ልጠየቅ ምንድነው እሷን ብቻ ማስጨነቅ የሰው ነብስ መሰላቹ እንዴ በቃ ሀጂ ነገርኩህ"እያለ ሀጂ ላይ አፈጠጠ ሀጂ ፊታቸው እየተቀያየረ ሲመጣ ይታየኛል ቆጣ ባለ ድምፅ"ተረጋጋ ያናገረህ የለም ወይስ እጅህ አለበት ለነገሩ አንገት ደፊ ሀገር አጥፊ አይደል ሚባለው"እያሉ አማርን ሽቅብ እያዩት ወደኔም መለስ ብለው አዩኝ ከዚህ በላይ ልሰማቸው አልፈለኩም ግን ማስረዳት ስላለብኝ ሁሉንም በዝርዝር አስረዳኀቸው አማርም ደገመላቸው ግን ፈፅሞ ሊያምኑን አልቻሉም ሀጂ ከተቀመጡበት ተነስተው ወደ በሩ ሲሄዱ ሁሉም ብድግ አለ እኔ ግን የሀጂ እንዲ መሆን አስደንግጦኝ ደንዝዣለው ኢነብ ስትወጣ ቀስ ብላ ወደኔ እያጎነበሰች "በአላህ ቂም እንዳትይዥበት ታቂው የለ እያረጀ ነው"ብላኝ ወጣች ትንሽም ቢሆን ፈገግ አስብላኛለች እናቴ ከበር ሸኝታቸው ተመልሳ እንደ መቀመጥ እያለች "በተከበርኩበት እንደው ታስንቂኝ መርዝ ይሁንብሽ ብሩ አይጥቀምሽ እሳት ይሁንብሽ"እያለች የ እርግማን መአት ስትደረድር ቦርሳዬን ይዤ ከቤት ወጣው የት እንደምሄድ አላውቅም ግን እግሬ እየተጓዘ ነው ከግማሽ ሰአት ብሀላ እንደመረጋጋት ስል የአክስቴ ሰፈር ደርሻለው እንዴት እንደመጣው ግን የማቀው ታሪክ የለምም ምርጫ ስላልነበረኝ አክስቴ ጋር ለመቆየት ወሰንኩ አክስቴም በፈገግታ አስተናገደችኝ የዛን ቀን ማታ አክስቴ እናቴ ነግራት ስለነበር ጠየቀችኝ እኔም ሁሉንም ነገር አብራራሁላት ግን ደስ የሚለው አክስቴ እኔን ማረጋጋት እንጂ ማጨናነቅ አልፈለገችም እና ታፅናናኝ ጀመር ግን አክስቴ በመሀል ዝምምም ትልና እንደ ድንገት በሽታው እንደተነሳ እብድ "ግን ሌላ አስቀምጣለው ምትይው ቦታ የለም?አስታውሺ"ትልና አሁንም ለረዥም ሰአት ዝም ትላለች ሲጨንቃት ነው መሰል እየደጋገመች ይቺን ቃል ትለኛለች የአክስቴ ነገር እያሳቀን የንዴት ሳቅ እየሳኩ "ባክሽ አክስቴ ሙድ አትያዢ ያልተፈለገበት ቦታ የለም እኮ"እላታለው ግን ደግማ ይሄንን ንግግር ትደግመዋለች አይ አክስቴ ሚስኪን እኮ ናት! አይነጋ የለምና ነጋ ጠዋት ተነስቼ ወደሱቅ ለመሄድ ስል አክስቴ ከእናቴ ጋር እደምታስማማን ነግራኝ አስቀረችኝ ከአክስቴ ጋር የቤቷን ስራ እንደጨረስን ወደኛ ቤት አመራን እኛ ቤት በር ላይ ልንደርስ ስንል የቤታችን በር ተከፈተ ቀጥ ብዬ ቆምኩ "ማነው?".......
የቤታችን በር እንደተከፈተ አማር እና ወጣቱ ልጅ ከኛ ቤት ተከታትለው ወጡ አማር በሀሴት እያየኝ "ፈርሁ ለምን አልመጣሽም?" አለኝ አክስቴ ስላለች ብዙም ላወራው አልፈለኩም በአጭሩ"ከአክስቴ ጋር ፕሮግራም ነበረን"ብዬው ወደ ውስጥ ገባው አማር አክስቴን ሰላም ብሏት ቆመው እያወራት ነው እናቴ ከሽንትቤት እየተመለሰች እንደ ሆነ ያስታውቃል እጇ ላይ ማንቆርቆሪያ ይዛ "እእእ ወይዘሪት ሄደሽ አልነበር ለምን መጣሽ"እያለች ወደኔ እየቀረበች ንግግሯን ቀጠለች "ደሞ እቃውን ካረግሽበት ሳታመጪ እዚች ቤት ማደር ሚባል ነገር እንዳታስቢ"ስትለኝ ይብሱኑ ደሜ ፈላ አክስቴ ከአማር ጋር የጀመረችውን መሬ ጨርሻ ወደቤት ስትገባ እኔና እናቴ እየተጨቃጨቅን አገኘችን ግንባሯን እየቋጠረች"ምንድነው ፈርሁሁ?"አለች ወደ እናቴ እያየች እናቴ ክንዴን በእጇ ይዛ "የሰው ንብረት ካላመጣች አይኗን ማየት አልፈልግም" ብላ ወደበሩ ወረወረችኝ አክስቴ እየበሸቀች "ምን መሆንሽ ነው ሰአዳ የገዛ አንድ ልጅሽን እዲህ ምታረጊያት"እያለች ጮኃችባት እናቴ ግን ከሀሳቧ ፍንክች አልል ስትል ከአክስቴ ጋር እስከመጣላት ደረሱ እና አክስቴ ቤቷ ይዛኝ ሄደች በነገታው ሱቅ ስሄድ ሀጂ የሉም ግን አዲስ ሰው ተቀጥሯል እየገረመኝ ከሱቁ ስወጣ ከአማር ጋር መንገድ ላይ ተገናኘን ትንሽ ቁጭ ብለን ካወራን ብሀላ አማረ ዝም አለ ዝምታው ይጨንቃል ምን ሆኖ ነው የሆነ ነገር መናገር እንደፈለገ ያስታውቃል አማር ቁና ቁና መተንፈስ ጀመረ ጨነቀኝ ስላልቻልኩ "አሚ በአላህ አስጨነከኝ መናገር ምትፈልገው ነገር እንዳለ ያስታውቃል ምንድነው?ንገረኘ"ብዬ ወጥሬ ያዝኩት አማር ቀና ብሎ ሳያየኝ "ፈርሁ"አለ"ወዬ አሚ በአላህ ልቤ በ ምላሴ ልትወጣ ነው"እያልኩ ለማሳዘን ሞከርኩ አማር አሁንም ቀና ብሎ ሳያየኝ "ግን እንቢ ካልሺኝ እራሴን አጠፋለው"ሲለኝ ከተቀመጥኩበት ብድግ ብዬ ቆምኩኝ ሰው ሁሉ እኔን ሲያየኝ ደንግጬ ተቀመጥኩ እንባዬ እየመጣ "አሚ አላህን ፍራ የምን እራስ ማጥፋት ነው ንገረኝ ምንድነው?"ብዬ የጥያቄ መአት አወረድኩበት አማር ቀና ብሎ እያየኝ "ፈርሁ በቃ እንጋባ! ላግባሽ?!"እያለ ምላሼን አይኔ ውስጥ የሚያገኝ ይመስል አይን አይኔን ያየኛል እኔ አማር ባለው ሀሳብ ብሽቅ እያልኩ"ቆይ በዚ ሰአት እንደዚ አይነት ቀልድ ይቀለዳል"ብዬ መነጫነጭ ጀመርኩ አማር ቁም ነገር ሲያወራ ፊቱ ያስታውቃል "አቦ የምን ቀልድ ነው ማን ቀለደ ከምሬን ነው ፈርሁ"እያለ የጭንቀት ፈገግታ ፈገግ አለ አማር ከምሩን እንደሆነ ሲነግረኝ ደስስስ አለኝ የአለም ንግስት ነሽ እንደተባለች የአንዲት ተራ ሴት ልጅ ሹመት የተሰጠኝ ያህል ደስታዬ ገደብ አጣ እየፈገግኩ እሺታዬን ገለፅኩለት አማር በደስታ "እና ሽማግሌ መች ይላክ"አለኝ እንደ ድንገት ጭንቅላቴ ላይ አንድ ሀሳብ ድንቅር ብሎ መጣ ሀጂ እሳቸው እንዲ እየሆኑ እኛ ልንጋባ እያማረን ይቀራል "አሚ አይሆንም መጋባት እንችልም"ብዬ ቦርሳዬን አንስቼ ወጣው አማር አልተከተለኝም ስልክም አልደወለም 2 ቀን ሞላን ጨነቀኝ ለ አክስቴ ልነግራት ፈራሁ "ግን የምር እራሱን ያጠፋል? እንደዚህማ አያደረግም እና ለምን አልደወለልኝም?"እያልኩ አይምሮዬን በጥያቄ አጣደፍኩት እንደ ድንገት ወደ ሽንት ቤት ለመሄድ ከበራፉ ስደርስ አዙሮኝ ወደቅኩ በግምት 1፡00 ሰአት ላይ ይመስለኛል አይኔን ስገልፅ እናቴ ያዙኝ ልቀቁኝ ትላለች አክስቴ እጄን ይዛ ትንሰቀሰቃለች ጎረቤቶችም አሉ ምንድነው ለምንድነው ሚያለቅሱት ትንሽ ከማደንዘዣዬ ስነቃ እጄ ላይ ወርፌ ተሰክቷል ከመርፌው ቀ
408 viewsΜαμε, 08:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-30 21:31:00 ወርቁን ማን ሰረቀው
ክፍል ሰባት
(ነኢማ ኸድር)

......እኔኮ አልጠላህም ግን በቃ እኔ ስለማይመቸኝ ነው ምንም ጥቅሙ አይታየኝም"ብዬው መስኮቱን ከፈትኩት ጭንቀት ይሁን......እያላበኝ ነው አማር ወደኔ እየዞረ "ቆይ እኔ ሀራም(አምላክ ማይፈቅደውን)ነገር ጠይቄሻለው ደሞ ምኑ ነው ማይመችሽ ትዳር? ሰበብ ስታጪ ነዋ"እያለኝ አይኔን ያየኛል አማርና እኔ ሳናስበው እየተቀራረብን መጣን እንደባለፈው ግን ስሜታችንን መግታት አልቻልንም ይበልጡኑ መቀራረብ ጀመርን አማር ስሜቱን መቆጣጠር አቅቶታል እኔም መከልከል አላስቻለኝም የአማር ከንፈር ከንፈሮቼን ሲነኩ መላ አካሌን ነዘር አማር ስሜቱ ቱግ ሲል ይታወቀኛል እጆቹን ትከሻዬ ላይ እንዳደረገ ስልኬ ጠራ ከሰማይ መብረቅ የወረደ ያህል ድንቅጥ ብለን ተላቀቅን አማር ባለጌ ሆኖ አይደለም ግን ማንኛውም ሀይማኖተኛ ወንድ ቢሆን እንኳ የሚወዳትን ሴት ሲያገኝ ስሜቱን ለመግታት እንደሚቸገር አውቃለው ስልኬን ሳየው እናቴ ናት በር አካባቢ ስለነበርኩ ሳላነሳው ከመኪናው ወረድኩ እናቴ ተጨንቃ ስለነበር ገና አንዴ እንዳንኳኳሁ ነበር በሩን የከፈተችልኝ ጭንቀት በተሞላበት መንፈስ"ምን ሁነሽ ነው ሰው ያስባል አትይም እስከዚህም ድንጋይ ሆነሻል"ብላ ስትናገረኝ ሰበብ ሆነኝና መነፋረቅ ጀመርኩ እናቴ ግራ ተጋብታ አይን አይኔን እያየች "ችግር አለ ማን ምን አድርጎሽ ነው? ንገሪኝ?" ብላ እሷም ማልቀስ ጀመረች የተፈጠረውን መናገር ስለከበደኝ በሷ ንግግር ሆድ እንደባሰኝ አስመሰልኩና ወደ ቤት ገባን የሰው ፊት ማየት አስጠላኝ ወደ ክፍሌ ሄድኩና መንሰቅሰቅ ጀመርኩ እንዴት የጌታችንን ድንበር ተላለፍን?ቆይ እንዴትስ ደፈርነው? እያልኩ እራሴን መውቀስ ጀመርኩ ከአልጋዬ ጎን ወደ ተቀመጠው ትንሽዬ የመፅሀፍ ማስቀመጫ ላይ እስክቢርቶ እና ደብተር አንስቼ ግጥም ነገር መፃፍ ጀመርኩ!
የገባሁኝ ለታ!
ነይ ላድርስሽ ብለህ ያኔ ስትጠራኝ
"ወዳንተ ባልመጣው እግሬን በሰበረኝ።
.......ብዬ ሳልጨርሰው ስልኬ ድምፅ አሰማ መልእክት ነበር ቶሎ ብድግ አድርጌው መልእክቱ ውስጥ ገባው አማር ነበር መልእክቱ ግን ግጥም ነበር እንዲ ይላል
ምነው ባላወኩሽ!
ምናለ ባላቅሽ ምነው ባላየሁሽ
ስሜቴ አቅልጦኝ እንደዛ ስሟሽሽ
ደሞኮ ቅሌቴ እጄን መዘዝኩብሽ
እሳት ሲያንሰኝ ነው እንደው እንደው በተቃጠልኩ
ድንበሩን አስጥሼሽ ይኸው ላንቺም ተረፍኩ
ግን አይቶን ይሆን የ ፍጡራን መንጋ
በስሜት ነበልባል እንዲያ ስንጋጋ
ፍጥረትንስ ተይው ከኛ እንኳን ይብሳል
ግን ፍጣሪዬ እንዲህ ይታገሳል
ድንበሩን ስንዘል ለምን ዝም ይለናል

"መጨረስ አልቻልኩም ግን ስለተፈጠረው ነገር ሁሉ ይቅርታ ጥፋቱ የኔ ነው!"ይላል ትንፋሼ እስኪቆራረጥ እያለቀስኩ አምላኬን ይቅርታውን ተማፀኩ ትንሽ ስረጋጋ ቅድም ወደ ጀመርኩት ግጥም ተመለስኩ....
አይነጋ የለምና እንደ ምንም ነጋ ከእንቅፌ ተነስቼ ቁርሴንም ሳልበላ ወደ ስራ ሄድኩ ሱቅ እንደደረስኩ ሀጂ ከባለፈው ወጣት ጋር ውጪ ላይ ተቀምጠዋል እንዴ በዚ ጠዋት ምን እየሰሩ ነው?አጠገባቸው ደረስኩ ሀጂን ደፍሬ ቀና ብዬ ማየት ከብዶኝ "ወደውስጥ ለመግባት አንድ እግሬን እያነሳው "ደና አደራቹ ሀጂ ብዬ ወደ ባንኮኒዬ ሂድኩ ትንሽ እንደተቀመጥኩ ሀጂ "ፈርሁ ነይ ወደዚ ይህን እቃ አስገቢና ቦታ ቦታ አስይዙት"ብለው ከወጣቱ ጋር ጨዋታቸውን ቀጠሉ እኔ ግን ውስጤ ላይ ምንም ሰላም የለም ጭንቅ ጭንቅ ይለኛል ከኸድር ጋር እቃዎቹን እያስተካከልን ሳለ እንደ ማዞር ሲያረገኝ እዛው ቁጭ አልኩ ኸድር ደንግጦ "ፈርሂን ደ ና ነ ሽ ኮ ኮ ኮመመሽ ወይ ወ ወ ወደ ቤት ለምን አቴ ቴ ጂም"ብሎኝ ከተሰቀለበት መሰላል ወርዶ ውሀ አመጣልኝ ትንሽ ሻል እንደማለት ሱለኝ ተነስቼ ከኸድር ጋር መስራት ጀመርን ኸድር አንደኛውን መደርደሪያ ሞልቶ ስለነበር ወረደና ወደ ጀርባ በኩል አዞረው ኸድር ወዳለበት ጀርባ ለመሄድ ስል አዞረኝና ተዝለፈለፍኩ ከ 1 ሰአት ቡሀላ ስነቃ ሆስፒታል ነኝ ሀጂ ወጣቱ አማር እና ኢነብ ከበውኛል ሁሉም ዙርያዬን ከበው ይመለከቱኛል የማያልፍ የለምና ይሄም ቀን አለፈ በሳምንቱ ስራ ገባው ሀጂ ፊታቸውን አጠቆሩብኝ ግራ ተጋባው ሰላምታ ብሰጣቸውም መልሳቸው ከአንገት በላይ ሆነብኝ ወደውስጥ ገብቼ ባንኮኒው ላይ ልቀመጥ ስል ሀጂ እየተቆጡ "አምኜሽ ነበር ታዴያ እንዴት እምነትሽን በላሽ ሁሉንም ነገር አማር ነግሮኛል አላምናቹም ሁለታቹንም እንደ ልጄ ባቀረብኩሽ ምላሼ ይህ ነው" እያሉ አንቧረቁብኝ ከዚህ በላይ መስማት አላስቻለኝም እና ጥያቸው ወጣሁ በር ላይ አማርን አገኘሁት በትከሻዬ ገጭቼው እየተነፋረኩ ወደ ቤት ተመለስኩ ሀጂ እንዲህ ሲናገሩ ሰምቼ አላቅም ታዲያ ዛሬ ምን ተገኘ እቤት እንደደረስኩ እናቴ ነብር ሆና ጠበቀቺኝ ገና በሩን ከፍቼ እንደገባው ከተቀመጠችበት ብድግ እያለች "ምነው አክብረው ልጄ ባሉሽ እኔኮ ምንም ያለ አባት ባሳድግሽም ባለጌ አርጌ አላሳደኩሽም ይህ ነው የ እናትነት ምላሼ"ብላ አመናጨቀቺን ንዴቴ ግንፍል ብሎብኝ "አዎ ይህ ነው ምላሼ ቆይ ሁሉም የራሱን ልጅ ጨዋ አርጎ ሚያየው ለምንድን ነው የገዛ ልጃቸው አብሮን አልነበር" እያልኩ ማልቀስ ጀመርኩ መናገር እስኪያቅተኝ!
እናቴ አሁንም ቱግ እንዳለች ንግግሯን ቀጠለች" አሁን ይመጡልሻል ትነጋገራያለሽ ግን አላህን ፍሪ በተከበርኩበት አታዋርጂኝ"ብላ ቁጭ አለች ወደክፍሌ ለመሄድ ገና እግሬን ሳነሳ የጊቢያችን በር ተንኳኳ....

ይቀጥላል....

➥ሼር እንዳይረሱ
JOIN ⇒ @mame_graphics
•┈┈┈┈•✿❥❥✿•┈┈┈┈•
440 viewsMame, 18:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-05 19:25:56 ወርቁን ማን ሰረቀው
ክፍል ስድስት
(ነኢማ ኸድር)

አማር ከሗላዬ ቆሟል አንዳች አስፈሪ እንስሳ እንዳየ ህፃን ክው ብዬ ቀረው አማር ከእጄ ቁልፉን ተቀብሎኝ እየቆለፈ "ለምን ፊቴን ማየት ከበደሽ መብትሽ እኮ ነው"ብሎኝ ቆልፎ ወደ መኪናው ሄደ እኔ አሁንም እንደ ደነዘዝኩ ቆሚያለው ከድንጋጤዬ መንፈስ የተላቀኩት በ መኪና ክላክስ ነበር አማር ነው እንድገባ ምልክት መሆኑ ነው እያንቀጠቀጠኝ ወደ መኪናው ገባው ግን ምን አስደነገጠኝ ? ምንም አላረኩ እያልኩ እራሴን ለማጋጋት ሞከርኩ አማር መኪናውን እንደጉድ እያበረረው በ 20 ደቂቃ ውስጥ እቤት በር ላይ አደረሰኝ ልወርድ የመኪናውን በር እጀታ ወደኔ ስስበው እንቢ አለኝ ለካ አማር ጋር ባለው መቆጣጠሪያ ሁሉንም በር ዘግቶታል ድንጋጤ መላ አካሌን ወረረው ወደ አማር በዝግታ ዞርኩኝ አማር ቀና ብሎ ሳያየኝ "ቆይ አንዴ ቅድም የተናደድኩ መስሎሽ ከሆነ የተናገርኩሽ አይደለም ተሳስተሻል ለራስሽ ብዬ ነው እሺ"ብሎኝ የመኪናውን ሎከር ከፈተው ለመውረድ እጀታውን እየሳብኩ "አንድ ቀን ትረዳኛለህ ብዬ" ልወርድ በሩን ከፈትኩ አማር በቅፅበት እጄን ያዘኝ ሰውነቴን የሆነ ነገር ሲወረኝ ይታወቀኛል ወደ አማር ስዞር አማር ፊት ላይ እንባ አለ ደነገጥኩ አማር እጄን እንደያዘ "እኔኮ ላግባሽ ነው ያልኩት ታዲያ ይሄ ጥፋት ነው ግን ለምን?"እያለ አይን አይኔን ያየኛል አማር እንደዛሬ አንጀቴን በልቶት አያቅም እኔም እያለቀስኩ የተፈጠረውን ነገር ሁሉ በዝርዝር ነገረኩት አማር በሩን እንድዘጋው እና ትንሽ እንድናወራ ጠየቀኝ ስላሳዘነኝ አላንገራገርኩም ሰኣቱ ግን 3፡40 ሞልቷል ቢሆንም ግን አማር በዚህ ስሜት እቤት መመለስ ስለሌለበት በሩን ዘግቼው ከቅድሙ ይበልጥ አብራርቼ ነገርኩት አማር ግን አሁንም ከፍቶታል "ታዲያ ለምን አላገባም አልሺኝ"እያለ አፈጠጠብኝ "አሚ እኔኮ አል.....

ይቀጥላል...

➥ሼር እንዳይረሱ
JOIN ⇒ @mame_graphics
•┈┈┈┈•✿❥❥✿•┈┈┈┈•
849 viewsMame, 16:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-02 14:51:17 ወርቁን ማን ሰረቀው
ክፍል አምስት
(ነኢማ ኸድር)

የሀጂ መኪና ተከፍቶ አማር ወረደ ኡፍፍፍፍ! ግን አማር በሀጂ መኪና ለምን መጣ አማር ወደ ውስጥ እየገባ "ዛሬ የሀጂን ዙፋን እኔ ልቆናጠጥ ነው"ብሎ እየሳቀ የሀጂ ዙፋን ላይ ተቀመጠ የቅድሙን ነገር እንድረሳው አማር የቆጥ የባጡን ሲያወራ እኔ ስገለፍጥጥ በመሀል "ቆይ ግን አሚ የሀጂን መኪና ይዘህ የመጣሀው ምን አይነት ድፍረት ነው"ብዬ ኮሶተር አልኩኝ የፌዝ መኮሳተር! አማር ድምፁን ጎርነን አድርጎ "ክቡርነቶ ዛሬ አይመጡም ማታ አምሽተን ከዘጋን ታክሲ ስለምናጣ እንዳደርሶት ነው"ሲለኝ ተያየንና ሳቅን እኔና አማር እንዲ ልንስቅ ቀርቶ ተግባብተን አውርተን እንኳን አናቅም በመሀል ሳቄን አቋርጬ "ግን አሚ በአላህ የጠፋው እቃ አስጨንቆኛል ወላሂ እንቅልፍ ሁላ መተኛት አልቻልኩም ደሞ ሀጂን በዚህ ነገር እምነቴን እንዲጠራጠሩ አልፈልግም ምን ላርግ በአላህ"ብዬው ወደሱ ዞርኩ አማር በጣም እንደተጨነኩ ገብቶታል "ደሞ 'ስትመጣ ፈርሂን እቃ ትሰጥሀለች ተቀበላት'ብሎኛል እሺ ምን እናድርግ"ብሎኝ አጠገቤ ወንበሩን አስጠግቶ ተቀመጠ "በቃ የተፈጠረውን መንገር ነዋ ያለን ምርጫ እሱ ነው"ብዬው ፊቴን ወደ መስኮቱ አዞርኩ እንባዬ ስለመጣ አማር ካየ እንዳይጨነቅ ብዬ ነበር አማር ስለገባው "እያለቀሽ ነው እንዴ የኔ አልቃሻ በይ እንባሽን ጥረጊ አታብዥው የሰው ነብስ መሰለሽ እንዴ አናታም"ብሎኝ ወደ በሩ ሄደ የ አማር ስድቦች ስድብ ሳይሆን ምርቃት ነው ሚመስሉት ስድቡ ሁሉ ያስቃል እስቲ ፍረዱ አናታም! ተብሎ ስድብ ምን የሚሉት ነው አማር በር ላይ ሆኖ "በይ መጣሁ እንዳይደብርሽ ፈታ እያልሽ ጠብቂኝ"ብሎ ወጣ እኔም አንዳንድ ያለቁ እቃውችን ዞር ዞር ብዩ እያየው በድንገት ከሗላዬ "ፈርሂን"የሚል የሚያምር የወንድ ድምፅ ጆሮዩ ላይ አቃጨለ ድምፁን ወደ ሰማሁበት አቅጣጫ ዞርኩ የባለፈው ልጅ የ ሀጂ የጓደኛ ልጅ እኔን ደሞ ታክሲ አጥቼ ያደረሰኝ ልጅ ነበር
እየተርበተበትኩ "አቤት ጠራሀኝ "ብዬ" አየሁት እንደ ደነገጥኩ ስላወቀ "ይቅርታ ስገባ የሆነ ድምፅ ማሰማት ነበረብኝ አይደል ይቅርታ ስለቸኮልኩ ነው"ብሎኝ ወደበሩ ሄደና እያንኳኳ "መግባት ይቻላል"ብሎ ሳቀ የሚስብ ፈገግታ! ነገረ ስራው አስቆኝ እየሳኩ "ይግብ "ብዬው መሳቄን ጀመርኩ ከመጀመሪያው ይበልጥ እየፈገገ "ስንት ነን"አለኝ የ ኢነብ ባሀሪ ተጋብቶብኝ ነው መሰል ሳቄን ለቀኩት አማር ከውጪ ሆኖ "ማነው ባክሽ እንዲ የሚያስካካሽ" ብሎ ወደ ውስጥ ሲገባ የማያቀው ሰው ጀርባውን ሰቶት አገኘ እያየሁት ፊቱ ተቀያየረ
ፊለፊቱ ስለነበርኩ በአይኑ"ማነው?"አለኝ ወጣቱ እንዴት እንደሆነ እንጃ ከሗላው ሰው እንዳለ አውቆ ዞረ አማር በጣም ተናዶ ነበር "ይቅርታ ረበሽኳቹ"ብሎን ወጣ ወጣቱና እኔ ግራ ተጋብተን ተያየን ወጣቱ ከተቀመጠበት እየተነሳ "sorry አላወቀኝም መሰለኝ ቆይ ላረጋጋው"ብሎኝ ወደውጪ ሲወጣ አማርን አጣውና ተመለሰ እኔም ዛሬ ሀጂ እንደማይመጡ ነግሬው እቤታቸው እንደሚሄድ ነግሮኝ ሄደ እኔ ግን በስርአቱ አልሸኘሁትም የአማር እንደዛ መሆን ቢያናድደኝም አስጨንቆኛል አማር የት ሄዶ ነው? የፈረደባቸው ሀጂ ጋር? ወይስ....? አማር ከሱቅ ከወጣ 2 ሰአት ሞልቶታል እስካሁን ግን አልመጣም ሰዐቱ አምሽቱ 1፡00 ሰአት ሆኗል ጨነቀኝ ስልኬን አውጥቼ ብደውልም ስልኩ ዝግ ነው 2፡00 ሰዐት ሞላ ሱቁን ዘግቼ እንዳልሄድ ደሞ ሀጂ አምሹ ብለዋል ምን ላርግ አማር ካልመጣ ደሞ ታክሲ አላገኝም በሀሳብ ስብሰለሰል ደንበኛወች እየመጡ አጣደፉኝ ሳላስበው ሰአቱ 3፡00 ሰዐት ሞላ ደሞ ዛሬ ኸድርም ሀጂን አስፈቅዶ ቀን ሙሉ አልመጣም እንደምንም የሱቁን መስኮቶች ዘጋግቼ በሩን እየቆለፍኩ ሳለ አማር...

ይቀጥላል..

➥ሼር እንዳይረሱ

JOIN ⇒ @mame_graphics
•┈┈┈┈•✿❥❥✿•┈┈┈┈•
1.2K viewsMame, 11:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ