Get Mystery Box with random crypto!

እባካችሁ ለልጆቿ እንድትኖር እንድረስላት ስሟ ወይንሸት ፀጋዬ ይባላል፡፡ ነዋሪነቷ በሀዋሳ ከተማ | ማህደረ ጤና☞

እባካችሁ ለልጆቿ እንድትኖር እንድረስላት

ስሟ ወይንሸት ፀጋዬ ይባላል፡፡ ነዋሪነቷ በሀዋሳ ከተማ ባህል አዳራሽ ክፍለከተማ ሀረር ቀበሌ ውስጥ በኪራይ ቤት ውስጥ ነው፡፡ በየሰው ቤት በእሳት እንጀራ በመጋገር እና ምሽት ላይ በየ መንገድ ዳር ቆሎ በመሸጥ የ11 እና የ10 አመት ልጆቿን እያሳደገች አልፎም ደግሞ እያስተማረች የነበረችው ወይንሸት አሁን አቅም ከድቷት በአልጋ ላይ ስቃይ እያሳለፈች ትገኛለች፡፡ በገጠማት የጡት እና የአጥንት ካንሰር ለልጆቿ በእሳት ተቃጥላ የዕለት ጉርሳቸውን ታቀርብ የነበረችሁ እናት ዛሬ ግን አይደለም ለልጆቿ ለራሷ መሆን አቅቷት ህክምና እንዳገኝ እርዱኝ ስትል ለኢትዮጵያ ህዝብ ተማፅኖዋን እያቀረበች ትገኛለች፡፡

እኔም እናንተ ደጋግ የሀገሬ ልጆች ወይንሸትን እንድትደግፏት እና ቢያንስ ለልጆቿ እንድትኖርላቸው ስል በእግዚአብሔር ስም ጥሪዬን አቀርብላችዋለሁ፡፡

ወይንሸት ፀጋዬን መርዳት የምትፈልጉ "በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በስሟ በተከፈተው የሂሳብ ቀጥር 1000256462528 እንዲሁም በቀጥታ በመደወል ወይንሸት በስልክ ማግኘት የፈለገ በ0934720273 እና የቅርብ አስታማሚዋ ማርታ መጃ ስልክ 0926044328 በመደወል ማግኘትም ሆነ መርዳት ይችላሉ፡፡

ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ታከለ

#ሼር በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ ለምስኪኗ እናት እንድረስላት !