Get Mystery Box with random crypto!

የዛሬ ደስታዬ በአብርሆት ቤተመጽሐፍት ❖ይህ ቦታ ብርሃን የሚገኝበት ቦታ ነው።አብርሆት ማለት En | ነገረ-ፍፃሜ(Eschatology)

የዛሬ ደስታዬ በአብርሆት ቤተመጽሐፍት

❖ይህ ቦታ ብርሃን የሚገኝበት ቦታ ነው።አብርሆት ማለት Enlightenment ብርሃን የሚገኝበት(በራ) የሚለውን ቃል ያመለክታል። ቃሉ ከነገረ-መለኮት ጋር ይገናኛል። አብርሆተ መንፈስ ቅዱስ።በቅርቡ በመንግሥታችን የተሰራው ትልቁ የጥበብ ቦታ አብርሆት Library። የእውቀት ወዳጆች እውቀትንና ጥቤብን የሚሸምቱበት ቦታ።ለእኔ ደግሞ ከጠበኩት ልዩ የሆነልኝ መንፈሳዊ ትላልቅ መፅሐፎች ተደርድረው ማግኘተ ነው። ከእውቀት ትልቁ እውቀት የተሰቀለውን ክርስቶስን ማወቅ ነው። በመጀመሪያ ዓይነ ውስጥ የገባው መፅሐፍ በወ/ዊ ፀጋአብ በቀለ የተፃፈልን "የኢትዮጵያ አብያተክርስቲያናት የህብረትና ዓለምን በወንጌል የመድረስ ጥር"የሚለው ድንቅ መፅሐፍ ነው።
ከዝህ መፅሐፍ ያነበብኩትን ትንቢታዊ መልእክት እነሆ

........በወንጌል ስም ራስንና ገንዘብን መስበክ ሌላ ወንጌል ነው። ሌላ ወንጌል ደግሞ ፀረ ወንጌል ነው።እውነተኛ ቤተክርስቲያን ደግሞ የፀረ ወንጌል ፀር ናት። ከእንግዲህ ኢየሱስን የማይገልጥ ኢየሱስ የማይከበርበት ኢየሱስ ከፍ ብሎ የማይታይበት ኢየሱስ በቃሉና በመንፈሱ ያልነገሰበት መድረክ ሆነ አገልግሎት ከኢትዮጵያ በስሙ ስልጣን የተወገደና የተገለበጠ ይሆናል። ምድርቷ የታረደውን በግ በከፍታ የሚታከብርበት በዓል ይሆናል። ኢትዮጵያውያን በወንጌል ለወንጌል በዓለም ይታወቃሉ ይፈልጋሉ። ይህ ዘመን ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የወንጌል እንቅፋት የሆኑ የኑፋቄ ትምህርቶችን፥ራስ ተኮር አካሄዶችንና አገልግሎቶቸን በቃሉ በማጥራት ወንጌልን በመንፈስ ቅዱስ ሀይል ለዓለም ህዝብ በመስበክ በገሀድ የምትገለጥበት መለኮታዊ የቀጠሮ ዘመኗ ነው። አሜን
ወንጌል ከኢትዮጵያ ለዓለም ሁሉ!!
አብርሆትን ይጎብኙ!!

@መብራቱ መንግሥቱ 2015 ዓ.ዓ አ አ ኢትዮጵያ
https://t.me/+UK-E6QjEaWz2OCgp