2022-07-31 07:15:54
ነገር አለ፤እርሱም፡-ሕዝብና አሕዛብ አንድ ሆነው ጌታን ለመ ከራ
መስቀል አሳልፈው እንደ ሰጡት፥አሕዛብና መናፍቃንም አንድ
ሆነው ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን ላይጥሉአት
እየታገሉአት፥ላትሞት እየገደሉአት መሆናቸውን ነው።እኛም
ለወዳጃችን ለቅዱስ ገብርኤል እንነግረዋለን።“የእግዚአብሔር
መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ያድ
ናቸውማል፤”ይላል።መዝ፡ ፴፫፥፯። -መናፍቃኑ፡-“ታቦት በቅዱሳን
ስም ለምን ይሰየማል? እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጠው አንድ
ታቦት ነው፥የተቀረው ከየት መጣ?”የሚል ጅል ጥያቄ
ይጠይቃሉ።ይህንንም የሚሉት፡-የሚነገራ ቸውን መልስ
ላለመስማት ጆሮአቸውን ደፍነው፥ላለመቀበልም ልቡናቸውን
አደንድነው ነው። ነገር ግን ይኸንን ጥያቄ
ለመጠየቅ፥በመጀመሪያ፡-ሙሴ የተቀበለውን ታቦት
መቀበል፥የእግዚአብ ሔርንም ቅዱሳን መቀበል
ይጠበቅባቸዋል።ተቀብለውም ከሆነ ይንገሩን።ምክንያቱም፡-የጌታ
ቃል ፡-“እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥እኔንም የሚቀበል
የላከኝን (አብን መንፈስ ቅዱስን) ይቀበ ላል።ነቢይን በነቢይ ስም
የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ጻድቅንም በጻድቅ ስም
የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል።ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ
ለአንዱ በደቀ መዝሙር ስም ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ
የሚያጠጣ፥እውነት እላችኋለሁ፥ዋጋው
አይጠፋበትም፤”ይላል።ማቴ፡፲፥፵።ጥያቄውን በጥ ያቄ ስንመለስ
ደግሞ፡-ሙሴም፥ ነቢያትም፥ሐዋርያትም ጽፈውልን የሄዱት
መጻሕፍት አንድ አንድ ቅጽ ብቻ ናቸው፥ታድያ ዛሬ ዓለምን
ያጥለቀለቁት ቅዱሳት መጻሕፍት ከየት መጡ? ብለን እንጠ
ይቃለን። -“ታቦት በቅዱሳን ስም ለምን ይሰየማል?” የሚለውን
ጥያቄ ለመመለስ ብዙ ድካም የሚጠይቅ አይደለም።መልሱ
አጭር ነው፥እርሱም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ያስተማረው ት/
ት ነው። “ኢተ አምሩኑ ከመ ታቦቱ ለእግዚአብሔር አንትሙ
ወመንፈሰ እግዚአብሔር ላዕሌክሙ? ወዘሰ አማ ሰነ ቤተ
እግዚአብሔር ሎቱኒ ያማስኖ እግዚአብሔር፥ወቤቱሰ
ለእግዚአብሔር አንትሙ ውእቱ፥ ወቅዱሳን አንትሙ፥ወኢታርኵሱ
ቤቶ ለእግዚአብሔር።እናንተ የእግዚአብሔር ታቦት(ማደሪያ፥
ቤት) እንደ ኾናችሁ አታውቁምን? መንፈስ ቅዱስ አድሮባችሁ
እንዳለ አታውቁምን? የእግዚአ ብሔር ማደሪያ የሆነ ሰውነቱን
በኃጢአት ያሳደፈውን ግን እግዚአብሔር ፈርዶ ያጠፋዋል፥እናን
ተስ የእግዚአብሔር ታቦት (ማደሪያ) ናችሁ፥ንጹሐን ክቡራን
ናችሁ፤”ይላል።፩ኛ፡ቆሮ፡፫፥፲፮።ስለ ዚህ፡-እንደ ሐዋርያው አማናዊ
ት/ት ቅዱሳን በአጸደ ሥጋም በአጸደ ነፍስም የእግዚአብሔር ታቦ
ታት በመሆናቸው፡-ታቦት በስማቸውይሠየማል። -“ድከም ያለው
አንድ እንጨት ያስራል፤”እንዲሉ፥የሚታደስ ነገር በሌለባት ቤተ
ክርስቲያን፡-“እና ድሳለን፤”ብለው መከራቸውን የሚያዩ የውስጥ
መናፍቃን ደግሞ፡-“የአዲስ ኪዳን ታቦት ኢየሱስ ነው፤” እያሉ
ለማደናገር እየሞከሩ ነው።“ለመሆኑ በቤተ ክርስቲያን የኢየሱስ
ክርስቶስ ያልሆነ ታቦት አለ ወይ?” ቢባሉ፥ካልለገሙ በስተቀር
መልሱን ያውቁታል።ቅዱስ ጳውሎስ እኮ፡-“እናንተ የእግዚአብሔር
ታቦት ናችሁ፤” ብሎ ጨርሶታል።ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ
እግዚአብሔር ነው። ዮሐ፡፩፥፩፣የሐዋ፡፳፥፳፰።ስለሆነም፡-
በቅዱሳን ስም የተሰየሙት ታቦታት ሁሉ የኢየሱስ ክርስቶስ
ናቸው።የተቀረጸባቸው፡-“አልፋ ወዖ፤” የሚለውም የኢየሱስ
ክርስቶስ ኅቡዕ ስም ነው።የኢየሱስ ክርስቶስ ስም ደግሞ፡-
በተዋህዶ የከበረ አምላክ ስም በመሆኑ፥ከስም ሁሉ በላይ የሆነ
ስም ነው፥ ኃይልና ሥልጣንም አለው።ቅዱሳን ሐዋርያት አያሌ
ተአምራትን በስሙ ያደረጉት ለዚህ ነው፥ ዛሬም በስሙ
ተአምራት ይደረጋል፥እየተደረገም ነው።“ኢየሱስ ክርስቶስ
ትናንትና ዛሬ እስከ ዘለዓ ለምም ያው ነው።”ዕብ፡፲፫፥
፰።ከስሙም ጋር፡-“ከመ ለስሙ ለኢየሱስ ክርስቶስ ይስግድ ኵሉ
ብርክ ዘበሰማያት ወዘበምድር፤ ሁሉ(መላእክትም የሰው
ልጆችም) ለኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይሰ ግዱ ዘንድ፤”የሚለው
ይቀረጽበታል።በመጨረሻም በዚያ ታቦት የተሠየመው ጻድቅ
ወይም ቅዱስ ስም ይቀረጻል።ምክንያቱም እግዚአብሔር ቅዱሱን
ታቦቱ አድርጎታልና ነው፥ቅዱሱም በብዙ ገድል
ተቀጥቅጦ፥ቅድስናን ንጽሕናን ገንዘብ በማድረግ ለእግዚአብሔር
ታቦቱ ሆኖ ተገኝቶአልና ነው።እንግዲህ፡-“ታቦቱ፡-ለምን የተክለ
ሃይማኖት፥ የገብረ መንፈስ ቅዱስ ተብሎ ይጠራል?” ማለት፡-
የኢየሱስ ክርስቶስ ስም፡-በልቡናቸው የተቀረጸላቸው፥ሰውነታቸው
ም የእርሱ ማደሪያ የሆነላቸው ቅዱሳን፡-ለምን ተክለ
ሃይማኖት፥ገብረ መንፈስ ቅዱስ ተብለው ይጠራሉ? እንደ ማለት
ነው።ታድያ፡-እነርሱ የኢየሱስ ታቦት(ማደሪያ)
በመሆናቸው፥የእነርሱን ስሞች አስቀርተን “ኢየሱስ” እያልን
እንጥራቸው? እኛስ የፈጣሪን ስም ለፍጡር አንሰጥም፥ እነርሱም
አይሹትም፤ እነርሱ የሚሹት፡-ገብረ ኢየሱስ መባልን
ነው።“ሐዋርያ ሊሆን የተጠራ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ጳውሎስ
በነቢያቱ አፍ በቅዱሳን መጻሕፍት አስቀድሞ ተስፋ ለሰጠው
ለእግዚአብሔር ወንጌል ተለየ፤” ይላል።ሮሜ፡፩፥፩ ። -የመናፍቃን
ዓላማ የቅዱሳንን ስም መፋቅ፥መታሰቢያቸውንም ማጥፋት
ነው፥ቀጥለውም የኢየሱ ስን ስም መፋቅ ነው።ይኸንንም፡-
በምዕራቡ ዓለም ባሉ ጌቶቻቸው ላይ አይተናል።የቅዱሳን ስም
እኮ በዚህ ዓለም ባለች ሰማያዊት ቤተ ክርስቲያን ብቻ ሳይሆን፡-
በልበ ሥላሴም የተቀረጸ ነው። በቅዱስ ዮሐንስ የራእይ መጽሐፍ
ላይ እንደተገለጠው፡-“በሕይወት መጽሐፍ መጻፍ፤”የተባለው
በልበ ሥላሴ መቀረጽን ነው።“ድል የነሣው እንዲሁ በነጭ
ልብስ ይጐናጸፋል፥ስሙንም ከሕይ ወት መጽሐፍ
አልደመስስም፥በአባቴና በመላእክት ፊት ለስሙ
እመሰክርለታለሁ።መንፈስ ለአብ ያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ
ያለው ይስማ፤”ይላል።ራእ፡፫፥፭፤፳፥፲፪።ከዚህም፡-ኢየሱስ ክርስ
ቶስ፡-ሕይወታቸውን ለሞት አሳልፈው እስከ መስጠት
ደርሰው፥በስሙ ለመሰከሩለት ቅዱሳን፡-በስማቸው እንደ
ሚመሰክርላቸው እንማራለን።በወንጌልም፡-“ስለዚህ በሰው ፊት
ለሚመሰክር ልኝ ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት
እመሰክርለታለሁ፤”ብሎአል።ማቴ፡፲፥፴፪።አበ ብዙኃን
አብርሃምን፡-“ስምህንም አከብረዋለሁ፥ለበረከትም
ሁን፥የሚባርኩህንም እባርካለሁ፥የሚ ረግሙህንም
እረግማለሁ፤”እንዳለው፥እነዚህ ኢየሱስ ክርስቶስ ያከበራቸው
የቅዱሳን ስሞች፡-በሰ ማይ ባለ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ
መሠረቶችም ላይ ተቀርጸዋል።“በምሥራቅ ሦስት ደጆች፥
በሰሜንም ሦስት ደጆች፥በደቡብም ሦስት ደጆች፥በምዕራብም
ሦስት ደጆች ነበሩ።ለከተማይቱም ቅጥር አሥራ ሁለት
መሠረቶች ነበሩአት፥በእነርሱም ውስጥ የአሥራ ሁለቱ የበጉ
(የኢየሱስ ክርስ ቶስ) ሐዋርያት ስሞች ተጽፈው(ተቀርጸው)
ነበር፤” ይላል።ዘፍ፡፲፪፥፪፣ራእ፡፳፩፥፲፫። -የቅዱሳን ስም እና
መታሰቢያ በመናፍቃን ወሬና ጥላቻ የሚጠፋ
አይደለም።ምክንያቱም በቤቱ ውስጥ የማይጠፋ ስም እና
መታሰቢያ የሰጣቸው እግዚአብሔር ነውና።በነቢዩ በኢሳይያስ
የትን ቢት መጽሐፍ እንደተጻፈው፡-“በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ
ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበ ልጥ መታሰቢያና ስም
እሰጣቸዋለሁ፤”ብሎአል።ኢሳ፡፶፮፥፭።ቅዱስ ዳዊት፡-“የጻድቅ
መታሰቢያ ለዘለዓለም ይኖራል፤”ያለው ለዚህ ነው።መዝ፡
፻፲፩፥፮።የሚጠፋው የእነማን ስምና መታሰቢያ እን ደሆነ ሲናገር
ደግሞ፡-“መታሰቢያቸውን ከምድር ያጠፋ ዘንድ የእግዚአብሔር
ፊት ክፉን በሚያደ ርጉ ላይ ነው፤”ብሎአል።መዝ፡፴፫
163 viewsቀሲስ ስንታየሁ የኔአባት, 04:15