Get Mystery Box with random crypto!

𝐔𝐁𝐔𝐍𝐓𝐔 𝐄𝐓𝐇𝐈𝐎𝐏𝐈𝐀𝐍𝐒

የቴሌግራም ቻናል አርማ kingnan — 𝐔𝐁𝐔𝐍𝐓𝐔 𝐄𝐓𝐇𝐈𝐎𝐏𝐈𝐀𝐍𝐒 𝐔
የቴሌግራም ቻናል አርማ kingnan — 𝐔𝐁𝐔𝐍𝐓𝐔 𝐄𝐓𝐇𝐈𝐎𝐏𝐈𝐀𝐍𝐒
የሰርጥ አድራሻ: @kingnan
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.06K
የሰርጥ መግለጫ

"ኵሎ አመክሩ ወዘሠናየ አጽንዑ"
“Prove all things; hold fast that which is good.”
ሁሉን ፈትኑ መልካሙንም ያዙ፤”

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-04-13 21:25:46 ማን ያውቃል ?

አንድ እድሜው የገፋ ገበሬ፡ እርሻውን የሚያርስበት አንድ ያረጀ ፈረስ ነበረው አንድ

ቀን ፈረሱ ከታሰረበት አምልጦ ወደ ጫካ ሸሸ። የገበሬው ጎረቤቶች በገጠመው መጥፎ እድል አዝነው ሲያጽናኑት

“መጥፎ አጋጣሚ ይሁን ጥሩ ማን ያውቃል?” ብሎ መለሰላቸው።

ከሳምንት በኋላም የጠፋው ፈረስ ብዙ የዱር ፈረሶችን አስከትሎ ከጫካው ተመለሰ። ይሄን ግዜ ደግሞ ጎረቤቶቹ በገጠመው ጥሩ እድል ደስታቸውን ገለጹለት።

“ጥሩ አጋጣሚ ይሁን መጥፎ ማን ያውቃል?” ነበር የገበሬው መልስ።

ከዚያ ደግሞ የገበሬው ልጅ፡ ከዱር ፈረሶቹ አንዱን ለማላመድ ሲሞክር፡ ከፈረሱ ጀርባ ወድቆ እግሩ ተሰበረ። የደረሰውን ክፉ አጋጣሚ ሁሉም ሲያማርር ገበሬው ግን

የተለመደ አስተያየቱን ደገመ፦

“መጥፎ አጋጣሚ ይሁን ጥሩ ማን ያውቃል?”
ከጥቂት ሳምንታት በኋላም የጦር ሰራዊቱ ወደ መንደሩ ዘልቆ፡ ጥሩ አቋም ያለውን ወጣት በሙሉ መለመሉ። የገበሬውን ልጅ ግን እግሩ በመሰበሩ ጥለውት ሄዱ።

ታዲያ ይሄ አጋጣሚ ጥሩ ነው ወይንስ መጥፎ? ማን ያውቃል?

https://t.me/kingnan
3.8K views18:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-09 00:01:09 ሌቦቹ .....


የታጠቁ ዘራፊዎች ናቸው፡፡ ወደ ባንክ ገብተው “አንድም ሰው እንዳይንቀሳቀስ! ገንዘቡ የመንግሥት ነው፤ ህይወታችሁ ግን የእናንተ ናት፡፡” ሲሉ ድምጻቸውን ከፍ 
አድርገው ተናገሩ፡፡ ሁሉም ሰው ነብሱን ለማዳን ሲል ወለሉ ላይ በደረቱ ተኛ፡፡ ይኼ “Mind Changing 
Concept” ይባላል፤ ከተለመደው ወጣ ባለ መልኩ የሰዎችን አስተሳሰብ መቀየር ነው፡፡ 

ጠረጴዛ ላይ ተደፍታ የነበረች አንዲት ሴት የማጉረምረም ድምጽ ስታሰማ፣ ከዘራፊዎች አንዱ 
ቆጣ ብሎ፣ “እመቤት እንደሰለጠነ ሰው አስቢ እንጂ ይህ እኮ ዘረፋ እንጂ አስገድዶ መድፈር 
አይደለም” አላት፡፡ ፀጥ አለች፡፡ ይሄ ደግሞ “Being Professional” ነው፤ በሰለጠንክበት 
ጉዳይ ላይ ብቻ ትኩረት ታደርጋለህና፡፡ 

ከዛ ዘራፊዎቹ ጉዳያቸውን ጨርሰው ያለምንም ችግር ወደ ቤታቸው ገቡ፡፡ ከዘራፊዎቹ መካከል ልጅ እግሩ እና የMaster of Business Administration 
ተመራቂው የተዘረፈው ገንዘብ እንዲቆጠር ሃሳብ አቀረበ፡፡ ነገር ግን በዕድሜ ታላቅ የሆነውና 
እስከ ስድስተኛ ክፍል ብቻ የተማረው ዘራፊ፣ በቁጣ “አንተ የማትረባ ደደብ! ይህን ሁሉ ገንዘብ ማን ይቆጥራል? ምናለፋህ ዛሬ ማታ በቴሌቪዥን ዜና ላይ ስንት እንደዘረፍን ይነግሩናል፡፡” ይኼ “Experience” ይባላል፡፡ ዛሬ ዛሬ በትምህርት ከሚገኝ 
ዕውቀት ይልቅ 'ልምድ' የበለጠ ዋጋ አለው፡፡ 


ዘረፋው ከተፈፀመ በኋላ፣ የባንኩ ማናጀር የባንኩን ሱፐርቫይዘር ጠርቶ በአስቸኳይ ፖሊስ እንዲጠራ ነገረው፡፡ ሱፐርቫይዘሩ ግን፣ “ቆይ ተረጋጋ! 
እየውልህ፣ መጀመሪያ ከካዝና 10 ሚሊየን አንስተን ለራሳችን እንውሰድ፡፡ ከዚያም ባለፉት ወራት የወሰድነውን 70 ሚሊየን እንጨምርበት፡፡ 
ለፖሊስ ሪፖርት ማድረግ ያለብን ይህን ገንዘብ ዛሬ ከተዘረፈው ጋር ደምረን ነው” አለው፡፡ 
ይኼ “Swim with the tide” ይባላል፡፡ የተፈጠረን አስቸጋሪ ሁኔታ ለራስ ጥቅም ማዋል እንደማለት ነው፡፡ ሱፐርቫይዘሩም እንዲህ ሲል ተመኘ “በየወሩ ዘረፋ 
ቢካሄድብን እንዴት መልካም ነበር!” 

በሚቀጥለው ቀን፡፡ ከባንኩ የተዘረፈው ገንዘብ 100 ሚሊየን እንደሆነ በቴሌቪዥን ዜና ተነገረ፡፡ ዘራፊዎች ደነገጡ፤ የዘረፉትንም መቁጠር ጀመሩ፤ ማመን 
አቃታቸው። ደግመው ቆጠሩ፤ ያው ነው፡፡ ትንሽ ቆይተው እንደገና መቁጠር ጀመሩ፤ ተመሳሳይ መጠን -20 ሚሊየን ብር ብቻ። በጣም ተናደዱ፣ “እኛ ህይወታችንን 
ለአደጋ አጋልጠን 20 ሚሊየን ብቻ ስናገኝ፣ የባንክ ማናጀሩ ቁጭ ብሎ 80 ሚሊየን እንዴት ያገኛል?” 
ከንፈራቸውን ነከሱ፣ ጠረጴዛውን በቡጢ ነረቱ፡፡ 

ታድያ ሌባ ከመሆን ብልጥና መማር ይሻላል ማለት ይህም አይደል? 

የማናጀሩ ፊት በፈገግታ እንደ ማለዳ ፀሐይ አብረቅርቋል፤ የደስታ ግምጃ አድምቆታል፡፡ በሽርክና ገበያው የተፈጠረበት ጉድለት ተሞልቶለታልና፡፡ 
ይኼንንም “Seizing the opportunity” ይሉታል፡፡

https://t.me/kingnan
5.0K views21:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-27 17:03:21 ግድ የለሽ አትሁን

ጎርፍ ሲወስድህ እያሳሳቀ ነው፤ ስንፍና በአንድ ቀን ከሰው በታች አያደርግህም፤ በየቀኑ የምታደርጋቸው ትናንሽ የስንፍና ውሳኔዎች ግን ተጠራቅመው ነገ ዋጋ ያስከፍሉሀል።

ከዛ ገቢህን ስታየው ያንስብሀል ይሄ አይገባኝም ትላለህ፣ ስራህን ስታየው ውጤት አልባ ልፋት ነው፣ በምድር ለመደሰት አልታደልኩም ማለት ነው እስክትል ድረስ ህይወት አድካሚ ትሆናለች።

ህይወትህን እንዲህ አርጎ የሚያበላሸው ለነገ የምታሳድረው ስራ፣ ምንም ችግር የለውም ብለህ የተውከው የቀን ግዴታህና የማይረቡ ትንንሽ ውሳኔዎችህ ናቸው። ግድየለሽ አትሁን ትንሹ ጥረትህ ነው ትልቁን ውጤት የሚያመጣው!

መልካም ምሽት
https://t.me/kingnan
5.5K views14:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-19 19:08:48 ብልህ ሰው የትም ቢሆን መፍትሔ አያጣም

በአንድ ከተማ የሚኖር አንድ በእድሜ የገፋ ሰው ነበር፡፡ በጓሮው በሚገኘውን ማሳ ቆፍሮ ድንች መትከል ፈልጎ እርጅና ተጫጭኖታልና አቅሙ አልፈቀደለትም፡፡ ሊረዳው የሚችለው ብቸኛ ልጁ ደሞ እስር ቤት ነው የሚገኘው፡፡ እናም አባት ለልጅ እንዲህ የሚል ደብዳቤ ፃፈ፡፡

"ውዱ ልጄ ምንም ጥሩ ስሜት አሸየተሰማኝ አይደለም፤ ምክንያቱም የድንቹን ማሳ መቆፈር አልቻልኩም፡፡ አለመቆፈሬን አልወደድኩትም፤ ምክንያቱም እናተህ አትክልት በጣም ነበር የምትወደው፡፡ አንተ እስር ቤት ባትሆን አውቃለሁ ትቆፍርልኝ ነበር ፤ አባትህ"

በቀጣዩ ቀን አባት አጠር ያለ ፁሁፍ ደረሳቸው፡፡ "በፈጣሪ ስም ይዤካለው አባ ጓሮውን እንዳትቆፍረው፤ ሽጉጡን የቀበርኩት እዚያ ነው"

ከሰዓታት በኀላ በደርዘን የሚቆጠሩ የFBI መርማሪዎችና ፖሊሶች የሽማግሊውን ጓሮ በሙሉ በቁፋሮ ምስቅልቅሉን አወጡት፤ ነገር ግን ምንም ሽጉጥ እዛ አልነበረም፡፡

አባት በጣም ግራ በመጋባት አጠር አድርገው ለልጃቸው ምን እንደተፈጠረ እና ቀጣይ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ፃፉለት፡፡

ልጅ "አሁን ድንችህን ትከል አባ፤ ከዚህ ሁኜ ላደርግልህ የምችለው ነገር ቢኖር ይህን ብቻ ነው" ብሎ ፃፈላቸው፡፡

ያለንበት ነባራዊ ሁኔታ እኛን ሊወስነን አይገባም!

ደስ የሚያሰኝ ምሽት ይሁንላችሁ

Join us
https://t.me/kingnan
6.2K views16:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-15 20:55:28 እምቢ ማለትን መልመድ

በህይወትህ ውስጥ እምቢ የሚለውን ቃል ማዳበር የግድ ይላል ። የማታምንበትን ነገር አድርግ ስትባል እምቢ ፣ የማይሆን ቦታ እንሂድ ስትባል እምቢ ፣ ሰዓት የሚሻማህን ነገር አድርግ ስትባል እምቢ በል ።

በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ ብትሆን በይሉኝታ እሺ አለማለትህን እርግጠኛ ሁን !

መልካም ምሽት
https://t.me/kingnan
5.5K views17:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-05 20:45:07 ታገስ

ሁልጊዜም በህይወት መነሻህና መድረሻህ ስታስበው ቀላል ነው፤ መሀሉ ግን አይነገርም! አየህ ፈተናው፣ ተስፋ መቁረጡና ከባዱ ጊዜ ያለው መሀሉ ላይ ነው። ይሄን ወሳኝ ጊዜ በጥበብ ልታልፍ የምትችለው በአንድ ነገር ብቻ ነው 'በትዕግስት '
ወዳጄ ታገስ አለበለዚያ ምንም ብትለፋ ህይወትህን አትቀይርም!

ውብ ምሽት ተመኘሁላችሁ
https://t.me/kingnan
6.0K views17:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-01 20:37:19
ብዙ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ነፃ የወጡበትን ቀን ያከብራሉ፣ እኛ ደግሞ ቀኝ ገዢዎችን ድል ያረግንበትን!

መልካም በዓል ወዳጆቼ።

https://t.me/kingnan
5.9K views17:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-21 16:55:53 የሕይወት_ስንቅ
"በመከራ ውስጥ ስታልፍ ወሳኙ ነገር ክብደቱ ቅለቱ ሳይሆን የምትሰጠው ምላሽ ነው!"
[አባት ለሴት ልጁ ካስተማራት]


#ልጅ ሕይወት ታክቷቷል። የኑሮ ውጣ ውረድ አድክሟቷል። ነባሩ ችግር ሲቀረፍ አዲሱ ይተካል። ነገሮች ሁሉ አስቸጋሪ ሲሆኑባት ሕይወት እንደሰለቻትና እንዳማረራት ለአባቷ ነገረችው።

#አባቷ ሼፍ (ምግብ አብሳይ) ነበርና ወደ ማእድ ቤት ይዟት ገባ። ሶስት ድስቶችን ውሃ ሞልቶ ማንደጃው ላይ ጣዳቸው። ከዚያም የመጀመሪያው ድስት ላይ #ካሮት፥ ሁለተኛው ድስት ላይ #እንቁላል፥ ሶስተኛው ድስት ላይ #የቡና_ፍሬ ጨመረበትና እሳቱ ላይ በደንብ አንተከተካቸው። [ይህ ሁሉ ሲሆን ልጅቷ ተመስጣ በዝምታ ትመለከተው ነበር።]

በመጨረሻም እሳቱን አጥፍቶ ካሮቱን እና
እንቁላሉን በማውጣት ዝርግ ሰሃን ላይ
አስቀመጠ። ቡናውን ደግሞ በስኒ ቀድቶ
አስቀመጠ። አባት ለልጁ ካሮቱን እንድትነካው አስጠጋላት። ልጅ ነካካችው እንደ ለሰለሰአስተዋለች።

አባት እንቁላሉን ሰብራ እንድትመለከተው
ነገራት። ሰብራ ተመለከተችው ከቅርፊቱ በታች ያለው ውስጠኛው ክፍል ጠንክሯል።

ቡናውን ፉት እንድትል አዘዛት ቀመሰችው ጣእሙ ድንቅ ነበርና ፈገግ አለች።

ልጅቷም አባቷ ለምን እንዲህ እንዳደረገ ግን አልገባትምና " አባቴ ምን ለማለት ፈልገህ ነው? ይሄ ከእኔ ጋር ምን አገናኘው? ትርጉሙን ንገረኝ አለችው?"

አባቷም እንዲህ አላት፦ " ልጄ ሶስቱም ነገሮች ተመሳሳይ ነገር ገጥሟቸዋል። ሁሉም በሚፈላው ውሃ ተቀቅለዋል። ነገር ግን የእያንዳንዳቸው ምላሽ የተለያየ ነበር።

ካሮቱ የቀድሞ ጥንካሬውን አጥቶ ደካማ ሆኗል። እንቁላሉ በላይኛው ቅርፊቱ የሚንተከተከውን ውሃ የተቋቋመ ቢመስልም ውስጠኛው ፈሳሹ ግን
በመኮማተር ጠጥሮ ነበር። የቡና ፍሬዎቹ ይለያሉ ምንም እንኳን ቢቀቀሉ ውሃውን መቀየር ችለዋል።

አንቺ የቱ ነሽ? መከራና ችግር ፈተና በርሽን ባንኳኳ ጊዜ እንዴት ነው ምላሽ የምትሰጫቸው? እንደ ካሮቱ እንደ
እንቁላሉ ወይስ እንደ ቡናው? በደንብ አስቢ።

ጠንካራ የምትመስይ መስለሽ ነገር ግን መከራ በመጣ ጊዜ እንደ ካሮቱ
ልፍስፍስ ሆነሽ ትገኛለሽ?

እንደ እንቁላሉ በቀላሉ ሃሞትሽ ፍስስ የሚል የሚኮራመት ልብ ያለሽና ውጫዊ ገፅታሽ እንዳለ ሆኖ ውስጥሽ ግን በምሬት የተሞላሽ ነሽ? ወይስ

እንደ ቡናው ፍሬ የቱንም ያህል ችግር፤ ፈተና፤ ስቃይ ቢገጥምሽ አስከፊ መከራ ቢደርስብሽ ጣእምና ቃናሽን በመለገስ አካባቢሽን የምትቀይሪ ነሽ? ራስሽን ተመልከቺው አንቺ የቱ ነሽ?

ልጄ ዋናው ነገር ምን መሰለሽ? ፈተናና
መከራ ሲመጣ ወሳኙ ነገር ክብደቱ ቅለቱ
ሳይሆን የምንሰጠው ምላሽና አቀባበላችን ነው የሚወስነው። " ሲል ስለ ሕይወት አስተማራት።

እስኪ ልጠይቃችሁ እናንተስ ፈተና፤ ችግር፤ ስቃይ፤ መከራ ሲገጥማችሁ እንዴት ነው ምላሽ የምትሰጡት እንደ እንቁላሉ ካሮቱ ወይስ እንደ ቡናው? የትኛውን ናችሁ?

https://t.me/kingnan
7.6K views13:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-14 17:11:54 ጥሩ ዛፍ ከተጠጋህ ጥሩ ጥላ ታገኛለህ

1)ጥሩ ዛፍ ከተጠጋህ ጥሩ ጥላ ታገኛለህ
ጥሩ ጓደኛ ከተጠጋህ መልካም ነገር ትማራለህ
2)ምቀኞች መብዛታቸው በስኬት መንገድ ላይ የመሆንህ ምልክት ነው
3)ወንድ ልጅ እናቱ በሕይወት እስካለች ድረስ ሕፃን ነው..ለእናቱ
4)በፈተና ላይ አለመታገስ ሌላ ፈተና ነው
ፈገግታ ቃላት የሌለው መልካም ንግግር ነው
5ካንተ የባሰ አለና አመስግን ፈገግ በል

6) በኃላህ የሚወጋህ ካለ አንተ ወደፊት የምትራመድ ነህ ማለት ነው
7) የተዋበ ንግግር ግልፅ የሆነን እውነት ሊሸፍን ይችላል
8) ለሌሎች ጥሩ ጓደኛ ሰትሆን ጥሩ ጓደኛ ታገኛለህ
9) ረዥም ምላስ አለው ማለት አጭር እጅ እንዳለው ያመላክታል
10) ሁለት ወፍ የሚያባርር ሁለቱንም ያጣል
11) የበጎች መንጋ ውስጥ መሪ ከምትሆን ከመንጋው የተነጠለ አንበሳ ብትሆን ይሻላል
12) ትንሽን ለመስጠት አትፈር ምንም አለመስጠት ከሱ የባሰ ነውና
13) የተሸናፊዉ ፈገግታ ያሸናፊውን ደስታ ይቀንሳል
14) የሁሉን ሰው ውዴታ ማግኘት ሊደረስበት የማይቻል ግብ ነው
15) ነፍስ በኩራት ስትሞላ ጎደሎ የመሆኗ መገለጫ ነው
16) ኩራተኛ ሰው ተራራ ጫፍ ላይ ሆኖ ሌሎችን ትንሽ አድርጎ እንደሚያይ ነው ነገርግን እሱንም ትንሽ አድርገው እንደሚያዩት አያውቅም
17) ብዙ ጊዜ በጉጉት ከምንጠብቀው ይልቅ ድንገት የምናገኛቸው ነገሮች ውብ ናቸው እኛ ከለፋነው ጌታ የፃፈው መልካም ነውና
18) ግኡዝ የሆኑት ውሃና አፈር ለእፅዋት አግልጋይ ናቸው ፤
እፅዋቶች ደግሞ ለእንስሳት ያገለግላሉ
እንስሳት ፣እፅዋትና ግኡዛን ደግሞ የሰውን ልጅ ያገለግላሉ ... በተቃራኒው
የሰው ልጅ ወደታች ወርዶ ለግኡዛን አገልጋይ (አምላኪ) መሆን ከጀመረ ያኔ ከነሱ የባሰ ይሆናል።
19) ሰውን ዛሬ ባየሁ ሁኔታው የነገውን አትናገር ነብያት በግ ጠብቀው ከዛ የሰዎች መሪ ሆነዋል
20) ለአንድ ጌታ ሲሰገድ፦ ፊት ወደመሬት ቢወርድም እውነታው ግን ወደ ሰማይ መውጣት ነው
21) የሰው ልጅ ለዘለዓለም እንደሚኖር ሆኖ ይለፋል አንድ ቀን የኖረ ሳይመስለው ይሞታል፨

https://t.me/kingnan
6.3K views14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-09 20:48:13 የአይምሮ ሰላም

ሁሉንም ለማስደሰት እንደሚጥር ሰው ከንቱ የለም! ሁሉም ሰው በተመሳሳይ ነገር አይደሰትም እኮ፤ በተለያየ ነገር ለሚደሰቱ ሰዎች ስንል ደግሞ እኛ እንደ ወረቀት መተታጠፍ የለብንም።

ህሊናችን የሚነግረንን አይምሮአችን የሚያዘንን ልባችንን በደስታ የሚቀበለውን ብቻ መርጦ ማድረግ፤ ያኔ ሰዎች ቢደሰቱም ባይደሰቱም ህሊናችን ግን ምን ነካህ እያለ አያስጨንቀንም። ወዳጄ ለህሊናህ ስትታመን ሁሌም ውስጥህ ሰላም አለ!
የተባረከ አዳር ይሁንላችሁ

https://t.me/kingnan
5.8K views17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ