2022-06-30 20:05:30
ሃናን
ክፍል-29
#የመጨረሻው_ክፍል
...ያ ሁሉ የሆን በምክንያት ነበር (የፃፍኩት) ምን አልባት በሆነው ነገር ጥቂት ሰው ትምህርት ወስዶበት ሊሆን ይችላል...
...ፍቅር የልብ መገጣጠም ነው! የምታፈቅራት ሴት እንደምታፈቅራት ባትነግራት እንክዋን እስዋም የምታፈቅርህ ከሆነ ፍቅርህ ይገባታል ከአይኖችህ ታነባለች በድምፅህ ቅላፄ የፍቅርህን መጠን ታውቃለች "ምን ያህል ታፈቅረኛለህ?" ብላ አጠይቅህም ምክንያቱም በድምፅህ ቅላፄ የሚወጣው ቃላት ልብዋ ዘልቆ ይገባል በአይንዋ ሳይሆን በልብዋ ታይሃለች በልብ (ከውስጥ) የታየ እይታ ደሞ ምን ጊዜም ሃቅና ግልፅ ነው ለዛ ነው ብዙ ሰው ይሳሳትና በስህተቱ ልክ ልትቀጡት ስትፈልጉስህተቱን ለማስተባበል ይሞክራል "እኔኮ ለማለት የፈለኩት እንደዚ ነው" ወይም "እኔኮ ይሄን የምሰራው ለዚህ ብዬ ነው" በማለት ጥፋቱን ያስተባብላል የሱን ስህተት ከልብ ካያችሁት (በሱ ቦታ ሆናቹ ካያችሁት) ስህተቱ ስህተት ቢሆን እንክዋን ማስተዛዘኛ ትሰጡታላቹ "ይህ ያደረገውኮ ምን አልባት ለዚ ብሎ ይሆናል" ትላላቹ ይህ ነው የልብ እይታ ሚባለው ...(ከፈለጋቹ ፍልስፍና በሉተ)
...አንድ ያልነገርክዋቹ ነገር ላጫውታቹ በፊት ኮሌጅ እየተማርኩኝ ሳለው ጋደኛዬ አህላም ጋደኛችንን ሰሚራን ሁሌም በስህተት ትፈርጃታለች ከወንዶች ጋር ስትሆንና ስትሳሳቅና ስትጫወት ካየች ትናደድባታለች ትቆጣትም ነበር "ለምን ይህን ታደርጊያለሽ አላህን አትፈሪምን?" ትላታለች የሰሚራ መልስ ሁሌም "አንቺኮ አልገባሽም ተይው ምን አልባት አንድ ቀን ትረጂው ይሆናል" ትላትና ትሄዳለች አህላምም ተናዳባት ትተዋታለች ሁለቱም ግን በጣም ይዋደዳሉ እኔንም በጣም ይወዱኛል እንም እንደዛው...
...እንደነገርክዋቹ አህላም ሁሌም ሰሚራት ይህ ልክ አይደለም እንደዚ አድርጊ እያለች ትቆጣታለች ታድያ አንድ ቀን የኔን ልደት ለማክበር ይመስለኛል ቤት መተው ነበር ሰሚራ በለበሰችው ልብስ የተሸማቃለች የደበራት ትመስላለች እውነትም የለበሰችው ልብስ ይከብዳል ማለት ያን ያህል ባያጥርም አጥሮ ግን ነበር በማጠሩ ተሸማቃለች እንደ በፊቱ አትጫወትም ጥግ ቁጭ ብላ ነበር አህላም ያ ቀይ ፊትዋን እሳት አስመስላው ለሰሚራ እንዲ አለቻት "በለው ዛሬ ምነው ለቀቅሽ እንዴ? ምን አይነት አለባበስ ነው?" ብላ ልክ እንደናት ተቆጣቻት በዚ ጊዜ ሰሙ ተናዳ ከሳሎኑ ወጣች እኔም ለአህላም "ምነው አሁንስ አበዛሺው እንዴት እንደዚ ትናገሪያታለሽ ትንሽ እንክዋን ለሞራልዋ አትጨነቂም?" ብዬ ተቆጣዋት አህላምም "ሃኒ ወላሂ እንዲከፋትኮ አልነበረው የለበሰችው ልብስ የሙስሊም አደብ አይደለም በጣም አጥሯል ለዛ ነውኮ" አለቺኝ እኔም "እኮ እንደዚ አልነበረማ" ብያት ተነስቼ ወደ ሰሙ ሄዱኩኝ ሰሙን አይዞሽ ውዴ ብዬ አፅናናዋትና አቀፍጅዋት በዚ ጊዜ ልብ የሚነከ ፈፅሞ ያልጠበኩትን ንግግርን ነገረቺኝ፦
"ሃኒ ሳላውቅ ቀርቼኮ አይደለም ችግር ያለብኝ ሰው ነኝ ከወንዶች ጋር እንደዛ ምሳሳቀውና ምጫወተው ፈልጌው አይደለም ወንዶችን በጣም እፈራለው የሆነ ነገር ካረጉኝ ብዬ እሰጋለው የዘውትር ጭንቀቴ ወንዶች ካሁን አሁን ምን አረጉኝ የሚለው ነው ለዛ ነው ከወንዶች ጋር ቀርቤ እንደነሱ ምሆነው ቢያንስ እንክዋን እቺማ ዱርዬ ናት ብለው እንዲርቁኝ ወይም ስለኔ እንዳያስቡ ስለምፈልግ ነው...
...ዛሬ የለበስኩት ቀሚስ ደሞ በሰዎች እይታ ዱርዬ መስዬ ለመታየት ነው ምክንያቱም ለዱርዬ ሴቶች ማንም ቦታ አይሰጥም በተሌ ወንዱ" አለቺኝ በአነጋገርዋና በአስተሳሰብዋ በጣም አዘንኩኝ ሰሙ እንደዚ አይነት ሰው አትመስለኝም ነበር በራስ መተማመንዋ የገነነ ጀግና ሴት አድርጌ ነበር ምስላት ታድያ ያሰብኩት ያሰብኩት አልነበረም ሰሙ ሌላ ታሪክ ውስጥ ገብታ ነበር ...
...ለአህላምም ሁሉንም አጫወትኩዋት አህላምም ደነገጠች ያኔ ሳተውቅ በተናገገረቻት ነገር አዘነች አህላም አንባቢ ስለነበረች አንድ መፃፍ ሰጠቻት (ጠብታ ማር) የሚል ርዕስ ነበር ይህ መፃፍ ከአላህ በኃላ በራስ መተማመንዋን መለሰላት...
..ከሃሜቱ እንውጣ, ብዙዎቻችን የሆነ ጉድለት አለብን ያንን ለመሸፈን ብለን በዙ ያልተገቡና መሆን የሌለባቸውን ነገራቶች እናደርጋለን የምናደርገው ነገር ልክ እንሁን ወይም ስህተት አናውቀውም በቃ በሰዎች ፊት የበታችነት ስሜት እንዲሰማን አንፈልግም(ይህ ልክ ነው) ነገር ግን ከልክ ያለፈ ጥርጣሬና ፍራቻ ከውስጣችን እናውጠ ሁለተኛው ማንነታችንን እናዳምጠው ሁለተኛው ማንነታች ፍፁም ልክ ነው ሁለተኛው ማንነታችን መሪያችን ነው (ተረገግቶ አስቦ የተናገረ... ) ይባል የለ ስትረጋጋና ስታስብ ከሁለተኛው ማንነትህ ጋር ትነጋገራለህ ሁለተኛውም ማንነተህ ደሞ ቅኑን መንገድ ይጠቁምሃል...
የኔ ታሪክ እዚ ጋር አብቅቷል ማናችንም መጀመሪያችን ላያምር ይችላል ይህ የኛ ጥፋት ሳይሆን የፈጣሪያችን ውሳኔ ነው ስለዚ መጨረሻችንን ለማሳመር ሁላችንም እንሞክር, እንጣር ወደ ጌታችን እንቅረብ እመኑኝ ወደ ጌታው የቀረበ ሁሉ ልዩዎች ናቸው ሁሉ ነገራችን እያማረ ይመጣል ውዶቼ አንሰሳት ማለቴ አይደለም ስህተትን አናብዛ ስህተቶቻችን መማሪያ ይሁኑን... ውድዋ እህቴ ውዱ ወንድሜ ሰለ ነጊያችን እናስብ ጊዜያዊ ነገር ሁሉ ለተራ ሰዎች እንጆ ለኛ አይነቱ (ለሙስሊም) የተገቡ አይደሉም ጌዜያዊ ነገር እንዳያምረን እንዳያታለንም...
#ተፈፀመ
አብራችሁኝ የቆያቹ ሁሉ ከልብ አመሰግናለው
የሃናን ታሪክ እንዴት ነበር? እስቲ በውስጥ መስመሬ ንገሩኝ ምን ተማራቹበት...?
@Nebiyat_M
ነገ በአዲስ ታሪክ "የሆለታው የምሽት ጉዞ" በሚል ከቀናቶች ባንዱ ቀን የገጠመኝን በመጀመሪያ ፁሁፌ እንገናኛለን መልካም አዳር ተመኘሁ
=========//////===========
ግሩፕፓችንን እና ቻናላችንን join አድርጉ
@kemtshafet_teg_group
2,900 በላይ አባል ያለው
@kemtshafet_teg
250 በላይ ሰብስክራይብ ያለው
========== **** ==========
ባለፈው ቃል በገባሁላችሁ መሰረት "የሆለታው የምሽት ጉዞ" ከቀናቶች ባንዱ ቀን የገጠመኝን የመጀመሪያ ፁሁፌን "የሃናን" እውነተኛ ታሪክ እንዳለቀ የሚጀመር ይሆናል አብራችሁኝ ቆዩ
270 viewsÑebiyat M., 17:05