Get Mystery Box with random crypto!

➪ የሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5 ኪ.ሜ ውድድር የፊታች እሁድ ይካሄዳል የ2015 ሳፋሪኮም ቅድሚ | ቅኝት በኳስ ሜዳ | Kegnit be Kuas Meda

➪ የሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5 ኪ.ሜ ውድድር የፊታች እሁድ ይካሄዳል

የ2015 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5ኪ.ሜ. ውድድር መጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ይካሄዳል።
ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጋር በመተባበር የተዘጋጀው “ቦታዬ ፣ መብቴ ፣ ድምፄ” በሚል መሪ ቃል ይከናወናል፡፡

• በዚህ ውድድር 15,000 ተሳታፊዎች ይገኙበታል፡፡
• ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ በሚገኙ የዳሸን ባንክ ቅርንጫፎች እንዲሁም በአሞሌ ሞባይል መተግበሪያ ለአንድ ተሳታፊ 450 ብር በመክፈል መመዝገብ ይቻላል፡፡
• ክፍያ ካጠናቀቅሽ በኃላ ምዝገባ የሚካሄደው በቀላሉ ካለሽበት ቦታ ሆነሽ በታላቁ ሩጫ የመመዝገቢያ telegram Bot ነው። @GREATETHIOPIANRUNBOT

• ተወዳዳሪዎች ሲመዘገቡም 20ኛ ዙር ውድድር የክብር አጋር ሆነው ከተቀላቀሉት ስንቅ ማልት፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ዳሸን ባንክ እና ኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት የተለያዩ ስጦታዎችን የሚያገኙ ይሆናል፡፡

• አትሌት መሰረት ደፋር ከ35 ደቂቃ በታች ለሚገቡ ተሳተፊዎች የሰርተፊኬት ማበረታቻ የምታበረክት ይሆናል፡፡
• የዘንድሮ ውድድር ከጤና ሯጮችም በተጨማሪ የሴት አትሌቶች፤ ተምሳሌት ሴቶች፤ የአምባሳደሮችና የአካል ጉዳተኞች ውድድርን ያካተተ ነው፡፡
• ዘንድሮ ከቲሸርትና ከሜዳሊያ በተጨማሪ ስጦታ በሽ፤ ቦርሳ፤ሎሽን፤ ባንዳና ከቲሸርቱ ጋር አብረው የሚሰጡ ይሆናል፡፡
• ለበለጠ መረጃ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ቢሮ 0116635757 ላይ መደወል ይቻላል፡፡

ቅኝት በኳስ ሜዳ