ኡመድ ኡኩሪ ብሔራዊ ቡድኑን ተቀላቅሏል በኦማን ሊግ ለአል-ሱዋይቅ ክለብ በመጫወት ላይ የሚገኘው ኡመድ ኡኩሪ በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ጊኒን በሚገጥመው ስብስብ ውስጥ ከተካተቱ 23 ተጫዋቾች መካከል አንዱ እንደሆነ ይታወቃል። ኡመድ ክለቡ አል-ሱዋይቅ ከትናንት በስቲያ አል ባሻይርን 4-2 ባሸነፈበት የሊግ ጨዋታ ላይ አንድ ጎል ማስቆጠር የቻለ ሲሆን በቀጥታ ወደ ሞሮኮ በማምራት በዛሬው ዕለት ካዛብላንካ የገባው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ስብስብን ተቀላቅሏል። የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን 981 views20:41