Get Mystery Box with random crypto!

Daniel: † † እንኳን ለኢትዮዽያዊቷ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል | ✞ገድለ ቅዱሳን✞

Daniel:
† † እንኳን ለኢትዮዽያዊቷ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። † †

† † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! † †

† † እመ ምዑዝ (እም ምዑዝ) † †

††† ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ሐዋርያዊት: ጻድቅትና ሰማዕት ናት::
ይህስ እንደምን ነው ቢሉ:-
=>ወር በገባ በ29 በቤተክርስቲያናችን ታስበው
ከሚውሉት እግዚአብሔር አምላክ ቃል ኪዳን ከገባላቸው
(ከሰጣቸው) እናቶች ኢትዮጵያዊቷ ሰማዕትና ጻድቅት
ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ (እመ ምዑዝ) ትገኛለች::
ፍቅርተ ክርስቶስ (እመ ምዑዝ) ማን ናት? ምን ቃል ኪዳን
ተሰጣት? ያደረገችውን ተጋድሎ በጥቂቱ እንመልከት:-
✞✞ ጻድቅን በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ
ይወስዳል፡፡ (ማቴ. 10፡40) ✞✞

=>በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት በመቂት ወረዳ ጥባ
ማርያም ቀበሌ ውስጥ ምን ታምር በመትባል ቦታ ላይ
በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኢትዮጵያዊቷ ሰማዕትና
ጻድቅ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ የተመሰረተቸው እመ
ምዑዝ ኪዳነ ምህት ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ አንድት
ገዳም ትገኛለች፡፡

+ይህች ገዳም ከአዲስ አበባ በደሴ ወደ ጎንደር
በሚወስደው መንገድ 665 ኪሎ ሜትር ከተጓዙ በኋላ
ገራገር (ፍላቂት) ከምትባለው ከተማ በመውረድ በእግር
2፡30 እንደተጓዙ ከ370 ዓመት ባለይ ያስቆጠረችውን
እመ ምዑዝ ኪዳነምህት ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ በአንድ
ቀን የሠራቻትና ለጌታ በአራቱም አቅጣጫ የሰገደችውን
ታላቅና ድንቅ ቤተመቅደስ ያገኛሉ፡፡

+የዚህች ታላቅ ገዳም መስራች ኢትጵያዊት ሰማዕትና
ጻድቅ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ በደቡብ ጎንደር ደራ ፎገራ
አንበሳሜ ወረዳ ልዩ ስሙ አቡነ ሐራ ገዳም አዋሳኝ ከተታ
ማርያም ተብሎ በሚጠራ ቦታ በሚያዚያ 4 ቀን ተፀንሳ
ታህሳስ 29 በጌታ ልደት ቀን ተወለደች፡፡

+አባቷ ላባ እናትዋ ወንጌላዊት የተባሉ እግዚዘብሔርን
የሚወዱ ትዕዛዙን የሚከብሩ ደጋግ ሰዎች ነበሩ፡፡
መሀን ሆነው ልጅ ባመውለዳቸው እያዘኑ ተግተው ወደ
እግዚአብሔር በመፀለያቸው ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስን
የመሰለች ልጅ: በፀሎትዋ ለሀገር ለወገን የምትበቃ
ሰጥቷቸዋል፡፡

+ከዚያም 80 ሲሆናት ለልጅነት ጥምቀት ወደ ቤተ
መቅደስ በወሰዷት ጊዜ ከጥምቀት በኋላ ስጋ አምላክ
ስትቀበል (ስትቆርብ) "ሕይወት የሆነውን ቅዱስ ስጋህን
ክቡር ደምህን የሰጠኸኝ አምላኬ ክብር ምስጋና ይግባህ"
ብላ አመስግናለች፡፡ ስመ ክርስትናዋ ማርያም ፀዳለ
ሲሆን የአለም ስሟ 'ሙዚት' ነው፡፡ ፍቅርተ ክርስቶስ
የምንኩስና (የቆብ) ስሟ ነው፡፡

+እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ አባ ዳንኤል ከሚባል
አባት መፅሐፍን እየተማረች ካደገች በኋላ ለአቅመ ሄዋን
ስትደርስ እናትና አባቷ ሊድሯት በመፈለጋቸው ዘርዓ
ክርስቶስ ለሚባል ከደጋግ ሰዎች ወገን ለሆነ ሰው
አጋቧት፡፡

+ማታ እንደ ሙሽሮች ደምብ ወደ ጫጉላ ቤት ሲገቡ
ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ዘርዓ ክርስቶስን "ወንድሜ ሆይ!
እኔ የእናት አባቴን ፍቃድ ለመፈፀም ነው እንጂ ስጋዊ
ሙሽራ መሆን አልፈልግም ፡፡ ፍላጎቴ የእግዚአብሔር
ሙሽራ መሆን ነው" በማለት ብታማክረው ቅዱስ ዘርዓ
ክርስቶስም ፀጋ እግዚአብሔር የበዛለት ሰው ነበርና "እኔም
እናት አባቴን ላክበር ፈቃዳቸውን ለመፈፀም ነው እንጂ
የስጋ ፈቃድ የለኝም በማለት ተነጋገሩ::

+በኋላ በአንድ ቤት ውስጥ ለቤተሰቦቻቸው: ለአገሬው
እንደ ባልና ሚስት ግን በንፅህና ለ40 ዓመት ሁለቱም
በድንግልና ኖረዋል፡፡

+ከዚያም በኋላ በእግዚአብሔር ፈቃድ ቅዱስ ሚካኤል
መጥቶ ወንድ ልጅ እንደሚወልዱ ቢግራቸውም ሁለቱም
"ይህስ አይሆንም" ብለው ለ40 ቀን በጾም: ፀሎት:
በትጋት ጸልየዋል፡፡ መልአኩ ተገልጦ "ይህ የእግዚአብሔር
ፈቃድ ነው ሁለታችሁም ድንግልናችሁ አይፈርስም ብሎ
ነግሮአቸዋል፡፡

+ከዚያም ወንድ ልጅ ወልደዋል:: ህፃኑ በተወለደ በ7
ዓመቱ በቅዱስ ሚካኤል እቅፍ ገነትን ለ7 ቀናት ከጎበኛት
በኋላ ወደ ምድር ሲመልሰው "በእናት አባቴ አምላክ
ይዤሃለሁ ወደዚች ወደ ከፋች ዓለም አትመልሰኝ" ብሎ
ቢለምነው ቅዱስ ሚካኤልም ከአምላክ ጠይቆ በብሔረ
ህያዋን የህፃናት አለቃ ተብሎ እንዲቀመጥ አድርጎታል፡፡
ስሙም ዳግማዊ ቂርቆስ ተብሏል፡፡

+ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶና ቅዱስ ዘርዓ ክርስቶስም ልጅ
ከወለዱ በኋላ እንደ ቀደሞው በቅድስና: በንፀህና ፀንተው
ኑረዋል፡፡ በዘመናቸው በኢትዮጵያ ነግሶ የነበረው አፄ
ሱስንዮስ ሃይማኖቱን ለውጦ 'ሁለት ባህርይ የሚሉ
ካቶሊኮችን በመቀበሉ ክርስቲያኖችን እየገደለ ነው' የሚል
ወሬ ሰምተው ወደ ንጉሱ በመሄድ ሳይፈሩ ስለ ተዋህዶ
ሃማኖታቸው በንጉሱ ፊት መስክረዋል፡፡

+ንጉሱም በጣም የበዛ መከራን አድርሶባቸዋል፡፡ መከራ
በበዛ ቁጥር እነርሱም እየፀኑ ተከታዮቻቸውንና የንጉሱን
ሠራዎቶች ሳይቀር አሳመኑ:: 60,000 ክርስቲያኖችም
ሰማዕትነትን ተቀብለዋል፡፡

+ንጉሱም በጣም የበዛ መከራ አድርሶባቸዋል፡፡ መከራ
በበዛ ቁጥር እነርሱም እየጸኑ ተከታዮቻቸውንና የንጉሱን
ሰራዊቶች እያሳመኑ ቢያስቸግሩ በሰማዕትነት አንገታቸውን
አስቆርቷቸዋል፡፡ አንገታቸውም ሲቆረጥ ከሁለቱም ደም
ውሃ ወተት ፈሷዋል፡፡

+በዚያን ዘመን ከእነ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ጋር
ሰማዕትነት ከተቀበሉት ውስጥ የማህበረ ስላሴው ጻድቁ
አምደ ስላሴ: የጎረጉር ማርያም አባ መርአዊ: የመሲ
ኪዳነ ምህረት እመ ወተት እና ከ60 ሺ በላይ ክርስቲያኖች
ሰማዕትነት ተቀብለዋል፡፡

+ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ አንገቷ ከተቆረጠና ሰማእትነት
ከተቀበለች በኋላ ወደ ምድር መልሶ አንገቷን ከቀሪው
የሰውነቷ ክፍል ጋር አዋህዶ ከአንቅልፍ አንደሚነቃ ሰው
ቀስቅሶ አስነስቷቷል፡፡
ከዚያም ከአቡነ ማርቆስ ስርዓተ ምንኩስናን በመቀበል
ዋልድባ ገዳም ለ4 ዓመት አገልግላለች፡፡

+ከዚህም ከ500 የሚበልጡ ተከታዮችዋን መነኮሳትን
አስከትላ በሰሜን ወሎ ቆቦ ወረዳ ወደምትገኘውና በፃድቁ
በአባ ጉባ ተመስርታ ጠፍታ ወደ ነበረችው ራማ ኪደና
ምህረት አንድነት ገዳም በመሄድ ገዳሟን አቅንታ: የወንድ
የሴት ብላ ስርዓት ሰርታ: ገዳሟን አስተካክላ: 500
የሚሆኑ አገልጋች መነኮሳትን አኑራ ወደ ኢየሩሳሌም ጉዞ
ጀምራለች፡፡

+በመንገዷም ላይ ሰውን የሚበሉ ወደ ሚኖሩበት አካባቢ
በመድረስ እነርሱም እርሷንና 60 የሚሆኑ አገልጋዮችዋን
ዓይኖቻቸውን በጉጠት በማውጣት ለ4 ወራት በጨለማ
ቤት ውስጥ ዘግተውባቸዋል፡፡ ከአራት ወር በኋላም በዓል
አድገው ለመብላት ከቤት ቢያወጧቸው መልካቸው እንደ
ፀሐይ የሚያበራ ቢሆንባቸው "አንቺ ሴት ምንድን ናችሁ?"
ብለው ጠይቀዋታል፡፡

+እርሷም ክርሰቲያን መሆናቸውንና እነሱ የስላሴ ሕንፃ
የሆነውን የሰውን ልጅ መብላት እንደሌለባቸው
ብትመክራቸው "ምን አንብላ?" ብለዋታል፡፡ እርሷም
ከራማ ኪዳነ ምህረት ስትነሳ የእህል ዘርን በአገልጋዮቿ
አሲዛ ነበርና ስንዴውን በአንድ ቀን ዘርታ: በቅሎ: ታጭዶ:
ደርቆ: ተፈጭቶ ለምግብነት በቅቷል፡፡

+እርሷ ቀምሳ ብታቀምሳቸው እንደማር እንደ ወተት
የሚጣፍጥ ሆኖላቸው በደስታ ተመግበውታል፡፡ ከዚያም
እንደዚህ እያደረጉ እየሰሩ እንዲበሉ አስተምራ: አስጠምቃ
ከ6 የሚበልጡ አብያተ ክርስቲያናትን አስተክላላቸዋለች፡፡