2022-07-07 14:30:34
እንኳን አስደንጋጭ የጅምላ የዘር ማፅዳት ጭፍጭፋ ቀርቶ ዶሮ የሞተበት እንኳን አይመስልም
ይህ ጠሚ በተደጋጋሚ እጅግ ዘግናኝ ጭፍጨፋዎችን ተከተሎ ዘግይቶ ወይም ተወትውቶ የሚያደርገው ንግግር ተመሳሳይ ሲሆን ሲሆን ፣ የንግግሩ ዋና ምስልም ጭፍጭፋው ማቅለል እና እንዲሁም እንደሚቀጥል ማረጋገጫ በመስጠት፣ ሁሉም ሃገር ላይ ያለ ችግር ነው የሚል አደምታ ያለው ነው። እጅግ በጣም አስደንጋጭ ነው ለሚያስተውል ሰው።
ጠ/ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ እየተፈፀመ ያለውን በመንግሰት መዋቅር የተደገፈ ጭፍጨፋ ከሌሎች አገራት ጋር በማነፃፀር ጭፍጨፋውን ኖርማላይዝ ለማድረግ የሄዱበት መንገድ ለገዳዮች ከለላ የሚሰጥና በቀጣይም ብዙ የተቀናጀ ጭፍጨፋ ሊኖር እንሚችል ጠቋሚ ነው።
ህዝብ መጠየቅ ያለበት በዘር ማጥፋት ወንጀል ይሄን ጠሚ እና የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሽመልስ አብዲሳን በሁሉም መንገድ ከስልጣን ወርደው ለፍርድ እንዲቀርቡ መጠየቅ እና መታገል ነው።
እንደነዚህ አይነት ከሰብዓዊነት የራቁ ለህዝብ ክብር የሌላቸው ወይ አያፍሩ አሊያም ህዝብን የማይፈሩ በነሱ ቤት አራዳ መሆናቸው ነው ግን ጭልጥ ያሉ ሰገጦች በእውነት ላሉበት ቦታ አይመጥኑም አይገባቸውም፣ አቅምም የላቸውም።
ተጠያቂነት እስከሌሌ ድረስ ጭፍጭፋው እና እልቂቱ ይቀጥላል። በደረጃ መጠየቅ ያለባቸው ሽመልስ አብዲሳ እና ጠሚው ናቸው። በዘር ማጥፋት ወንጀል ሊጠየቁ ይገባል።
260 views11:30