2022-07-20 22:09:19
መሻዒኾቻችን መከታዎቻችን!
ከእናቱ እቅፍ ተጠልሎ በንክብካቤ እንዳደገ ልጅ።በሼኾቹ ጉያ ተሸሽጎ፣ከበርካታ ኣጥፊ ክስተቶች ተጠብቆ የኖረ ማሕበረሰብ።እሱ በተደላደለ መኝታ አርፎ እነሱ ስለርሱ የሁለት ሀገር እጣ በመጨነቅ፣ እንቅልፍ ኣጥተው፣ለይሉ ስለሱ ሰላም በመብሰክሰክ የሚያሳልፉ።«አሏህዬ! ልጄን/ወገኔን ኣደራ!»ማለትን የዘወትር ልማዳቸው ያደረጉ።
የነፍሳቸውን ፍላጎት ቀብረው ስለ ዑመት መፃዒ ህልውና ተጠብበው ሌት ተቀን ከ ኻሊቅ ጋር የሚመክሩ።
በፀሎታቸው ሐገርን፣ወገንን፣ትውልድን ኣፅንተው ያቆሙ የአሏህ ሰዎች አሉ።ነበሩም…ይኖራሉም!
ከእያንዳንዱ ግለሰብ ስኬት ጀርባ ያሉ መከታዎች ናቸው።
ከበረከታቸው ዘርፈ ብዙ በሆነ መልኩ ተቋዳሽ ያልሆነ የለም።እልፎችን ከቁርዓን ንባብ ጅማሮ አሊፍ ከማለት ኣንስቶ፣እስከ ልሒቅነት ደረጃ አድርሰዋል።ከዝንጉ ሙስሊምነት ወደ መናኝ የምንፍስና ሂወት ኣልቀዋል።ከተራ አኗኗር ተነስቶ የተድላ ሒወትን እስከ መምራት።በሀገረ ሐበሻ አበው ሱፍዮች ያልተገራ ምዕመን የለም።አሁንም በግልፅም ሆነ በድብቅ ማህበረሰባቸውን ካለ ምንም ዓይነት ምድራዊ ክፍያ ህዝባቸውን ሳይታክቱ የሚያገለግሉ ደጋጎች ሞልተዋል።
በክፉ ጊዜያቶች የሚስኪን መሸሸጊያ ናቸው።የተራበ ህፃን ወደ እናቱ እንደሚሸሽ ኹሉ ሙሪድም ወደ ሸይኹ ይሸሻል።
በኛ ግትል የማይሞከረ የችግር ዓለት ክምር በነሱ ዱዓ ይፈርሳል። ከ ኻሊቅ ጋር መምከር የዘወትር ተግባራቸው ነውና ከችግሮች መውጫ ዘዴያቸውን ያቀብሉም ዘንድ ወደነሱ መዞር ያሻል።እነሱን ስንጠጋና ስንፈልጋቸውም ሁል ጊዜ ለሀጀታችንና፣ለግል ፍላጎታችን ማስተናበሪያነት፣ወይም ለቁሳዊ ዓለም ተድላ ቢቻ መሆን የለበትም።ኣንዳንዴም ስለነሱ ችግር በመጨነቅ።ስለ ፍላጎታቸውና ስለ ጉድለታቸው በመጠየቅ።ኣብሮነትና ፍቅርን፣ክብርባ ያባትነት ፍቅርን በመስጠት የተባረከ ልጅ መሆን ዘርፈ ብዙ እድያዎችን የምንሸምትበት የብስለት መንገድ ነው።
ሼኾቻችንን፣የሀገር አባቶች፣የወደን ኣለኝታዎች የቀዬ አድባሮችን፣ቁጥብና አቅጣቦችን፣አኸያር አብዳሎችን ባስደሰቱ ቁጥር የሚገኝ በረከት የትዬለሌ ነው።
ለወትሮም ለወገናቸው ሰላም ሲሉ እራሳቸውን ፊዳ ኣድርገው የህዝባቸውን ሰላም ኣስጠብቀዋል።ችግሮች እንዳይነኩን ሲሉ ችግሮችን ብቻቸውን ተጋፍጠዋል።እኛ ምቾትን ለምደን፣በነሱ ዱዓ ሰው ሆኖ መራመድን ኣግኘተን፣ድንገት የሆነ ነገር በራሳችን ወይም በመንገዳችን ላይ ሲደርስ የሰነፍ ለቅሶና የደካማ ትካዜ ሊወረን ኣይገባም።
ነፍሳችን በአምልኮ ማደስና ማጠንከር።በመንገዳችን የሚኖር ዘላቂ ፅናትን መላበስ።ኣዳባቶችን መከተል።በዱዓና በዚክር አብዝቶ መበርታት ከሁሉም አማኝ ሊለይ የማይገባ ልማድ መሆን ይኖርበታል።
አሏህ ሰላማችን ያብዛልን!ከፈተናም ይጠብቀን!
@jimi_yeabretu
40 viewsSalahadin Hulchafo, 19:09