2022-05-09 20:56:52
“I am” sent me to you “
እኔ ነኝ ልኮኛል (ያለና የሚኖር)
እግዚአብሔር ራሱን ለሙሴ ሲገልጥ ሙሴ ማን ለከህ ቢሉኝ ምን ልበላቸው አለ?
እግዚአብሔርም “እኔ እኔ ነኝ” ካለው በኋላ እኔ ነኝ ልኮኛል በላቸው አለው
ለካስ የ ኤሎሂም ስም “እኔ ነኝ” ኖሯል!!!
ይህ ማለት እግዚአብሔር የትላንት ወይም የ ነገ አምላክ ሳይሆን የ አሁን አምላክ ነው!!!
ምክንያቱም በ እርሱ አለም ለይ ትናንት ወይም ነገ ስለሌለ !!!
በ እግዚአብሔር አለም ላይ ያለው አሁን እና እና አሁን ብቻ ነው!!!
የ ሚገርመው በ አዲስ ኪዳንም እየሱስ መጣና ከ አብርሃም በፊት “እኔ አለሁ” አላቸው ፣ ነገር ግን ቃሉ መሆን የነበረበት አለሁ ሳይሆን ነበርኩኝ ነው (ሃላፊ ግዜ)(past tense)
ግን በሚገርም ሁኔታ “አለሁ” (present tense) ይላል ፣ ምክንያቱም እየሱስ የትላንት አምላክ ሳይሆን የ አሁን አምላክ ስለሆነ
እኔ እኔ ነኝ ማለት የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ ነው።
ለዚህ ነው ት.ኢሳ 47:8 ላይ… እኔ ነኝ ከእኔም በቀር ሌላ የለም…ብለሻል ብሎ እግዚአብሔር ባቢሎንን የሚቆጣው
በጣም የሚገርመው እግዚአብሔር የ አሁን አምላክ ስለሆነ የትኛውም የተበላሸብንን ትላንትና እንዲሁም ነገአችንን ሳይቀር ውብ አድርጎ ይሰራዋል!!! ሀሌሉያ
ለዚህ ነው በ ት. ኢዩ 2:25 የሰደድሁባችሁ ታላቁ ሠራዊቴ አንበጣና ደጎብያ ኩብኩባና ተምች የበላቸውን ዓመታት እመልስላችኋለሁ። …. የሚለው!!!
በጌታ በ እየሱስ ስም ተበላብኝ የላችኋቸው አመቶቻችሁ እንዲሁም ገና ያልኖራችኋቸው ቀኖቻችሁ ሁሉ ባለና በሚኖረው “እኔ ነኝ” በሆነው በ ኤሎሂም የተሰሩ ይሁኑ አሜን!!!
Kavod .T
https://t.me/Jesus_kingdom
428 views kabod , edited 17:56