።።።የጧት ስንቅ ...... በሕይወትህ ለሚሆነው ነገር አትዘን። የተፈጠርነውም ለመሞከር ነው። አላህ የምንታገስና የማንታገስ መሆናችንን ለመለየት በዚህ ላይ እንድናልፍ አድርጎናል። ነገሮችን አታካብድ። የደስታ ደመና ቅርብ በመሆኑ እንደሚዘንብ እርግጠኛ ሁን #ዶ/ኢብራሒም_አልፈቂ ➵ ሰዎች በጩኽት ያልሰሙህን ☞ አላህ በዝምታህ ይሰማሀል ይረዳሀል ምክንያቱም ልብህ ካንተ ይልቅ ለሱ ቅርብ ናትና። ➵ ከሰዎች ዘንድ ፈልገህ ያጣኸውን ☞ ከአላህ ዘንድ ሳትፈልግ ታገኘዋለህ ምክንያቱም አላህ ከምትፈልገው ይልቅ የሚያስፈልግህን ያውቃልና። "ደካማ ሰው ማለት ለስሜታዊ ዝንባሌ ተገዢ የሆነ (አንዳች የማይፈይድ ነገር ሳይሰራ) መልካምን ነገር የሚመኝና ከአላህ የሚጠብቅ ነው" [Tirmizy] :በጥረት መልካም ነገር ሲሳካልህ በአንተ ጥረት ሳይሆን በአላህ እርዳታ መሆኑን አውቀህ አመስግን። ማንም ሰው በራሱ አቅም ጭንቅላቱን ተሸክሞ የሚሄድ የለም መልካም ውሎ husnul_khuluk 575 viewsابن جمال, 04:32