Get Mystery Box with random crypto!

ኢስላማዊ እና ጠቅላላ እውቀት

የቴሌግራም ቻናል አርማ islamawe99 — ኢስላማዊ እና ጠቅላላ እውቀት
የቴሌግራም ቻናል አርማ islamawe99 — ኢስላማዊ እና ጠቅላላ እውቀት
የሰርጥ አድራሻ: @islamawe99
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 335
የሰርጥ መግለጫ

እየተጠያየቅን እውቀታችንን እናስፋ
ማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት ካላችሁ በዚህ ሊንክ ገብታችሁ
@islamawetube_bot ሀሳባቸሁን አካፍሉኝ ጥፋት ሰታዩብኝ አርሙኝ

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-07 09:21:09
29 views06:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 09:04:22 ወቅታዊ ማስታወሻ ለሙስሊሞች
ክፍል 2

ውድ ሙስሊም ወንድም ና እህቶች
ይህን ወቅታዊ ማስታወሻዬን ጥቂት ጊዜያችሁን ሰውታቹ እንድታነቡት አደራ አደራ እላለሁ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ አና በጣም አዛኝ በሆነው

በባለፈው ክፍል ስለ አረፋ ቀን ትሩፋቶች በበቂ ሁኔታ ለማየት ሞክረናል
ዛሬም ከባለፈው በቀጠለ መልኩ ባጭሩ የምንገልጽ ይሆናል

ዱዓ

በላጬ ዱዓ ማለት የዓረፋ ቀን የሚደረግ ዱዓ ነው። ረሱል ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም

አላህን የምንፈልገውን ነገር እንዲለግሰን
ከምንፈራው ነገር እንዲጠብቀን
ዱዓችንን እንደሚቀበለን እርግጠኛ ሆነን በመተናነስ ወደ እሱ መጣራት ማልቀስ መዋደቅ አለብን

ወንጀላችንን ሙሉ በሙሉ እንዲምርልን ወደ እሱ በመመለስ ማህርታን ከእሱ ብቻ መጠየቅ አለብን

በዛሬው እለት ማን ከሳሪ እንደሆነ ያውቃሉን?!

ዐብዱላህ ኢብኑ ሙባረክ ረሂመሁላህ እንዲህ ይላሉ ፦
"ዐረፋ ቀን ማምሻውን ወደ ሱፍያን ሰውሪይ ረሂመሁላህ መጣሁ። እርሱም በጉልበቱ ተንበርክኮ አይኖቹ እያነቡ አገኘሁት። ወደኔ ዞር ብሎ ተመለከተ። እኔም ፦"ዛሬ ቀን ለክስረት የተዳረገ ማን እንደሆነ ታውቃለህን?" አልኩት።
እርሱም ፦" እርሱ ያ ጌታው አይምረኝም ብሎ የተጠራጠረ ነው።" በማለት መለሰልኝ።"
ኢብኑ ረጀብ ሐንበሊይ /ለጧኢፉ አልመዓሪፍ

የታላቁ ዓሊም ሱፍያን ሰውሪይ ንግግር ምንኛ አማረ
ስለሆነም ሁላችንም በዱዓ መበርታት ግድ ይለናል

የዓረፋ ቀን የሚውለው ዕለተ ጁመዓ ሀምሌ 1 የዐረፋ ቀን ሲሆን በዓሉ ደግሞ ቅዳሜ ይሆናል ። የሚፆመው ጁመዓ ነው ማለት ነው።
ጁመዓ እና ዓረፋ ሁለቱም የራሳቸው የሆነ ትሩፋት አላቸው ከነዚህም ትሩፋቶች መካከል በዋነኝነት 2ቱም ዱዓ ተቀባይነት ሚያገኝባቸው ቀናቶች መሆናቸው ነው

ስለ ዓረፋ ቀን ዱዓ ነብያችንﷺ እንዲህ ይላሉ፦
"خير الدعاء دعاء يوم عرفة"
"ከዱዓ ሁሉ በላጩ ዱዓ ማለት የዓረፋ ቀን ዱዓ ነው"

ስለ ጁሙዓ ቀን ዱዓ ነብያችንﷺ እንዲህ ይላሉ፦
"فيه ساعة لا يوافقها عبد مسلم، وهو قائم يصلي، يسأل الله شيئًا إلا أعطاه إياه"
"በጁሙዓ ቀን ውስጥ የሆነች ሰዓት አለች በዚች ሰዓት አንድም ሙስሊም የሆነ ባሪያ ቆሞ እየሰገደ ለአላህ ምንም ነገር አይጠይቅም አላህ ያንን ነገር ቢሰጠው እንጂ

አላህ ﷻ የዚህን ቀን ትሩፋቶች ከሚያገኙ እና ወንጀላቸው ከሚማርላቸው ሰዎች እንዲያደርገን እለምነዋለሁ በመልካም ዱዓቹ አትርሱኝ

ይህን አንገብጋቢ ማስታወሻ ለምታውቁትም ለማታውቁትም ሙስሊም ለሆነ አካል እንድታሰራጬ እና የመልካም ስራ ተቋዳሽ እንድትሆኑ እጠይቃለሁ በሉ እንግዲህ ሼር ሼር ሼር
ክፍል አንድን በዚህ ያገኙታል https://t.me/tolehaahmed/143

ወሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ
طلحة أحمد
30 views06:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 19:54:53
#በአረፋ ዒድ ላይ ስለ ሚሰሩ መጥፎ ተግባሮችን ማስጠንቀቅ
በድጋሚ የተለቀቀ

በኡስታዝ ሻኪር ቢን ሱልጣን (ሀፊዘውላህ)

https://t.me/shakirsultan
40 views16:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 11:08:19 የኡድሒያን እርድ የሚመለከቱ ጥቂት ወሳኝ ነጥቦች
-
ኡድሒያ ማለት በዒደል አድሓ ቀን ወደ አላህ ለመቃረብ ታስቦ የሚታረድ እርድ ነው፡፡ ነብዩ ﷺ በተግባር ፈፅመውታል፡፡ መዲና ላይ አስር አመት ሲኖሩም ኡድሒያን ያርዱ ነበር፡፡ (ሚሽካት፡ 1475) እንዲፈፀምም አዘዋል፡፡ ስለዚህ አቅም ያለው ሰው ሊፈፅመው ይገባል ማለት ነው፡፡ ነብዩ ﷺ “አቅሙ እያለው ኡድሒያን ያላረደ ሰው መስገጃችንን እንዳይቀርብ” ብለዋል፡፡ (ከኡድሒያ ጋር የተያያዙ እጅግ አስፈላጊ ነገሮች፡-
የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት አለበት :-

1. የሚታረደው እንስሳ ከሚከተሉት የእንስሳት አይነቶች ብቻ መሆን አለበት፡- በግ፣ ፍየል፣ ከብትና ግመል፡፡
2. ከነዚህ እንስሳቶች የትኛውን ማረድ ነው የሚበልጠው? በቅደም ተከተል ግመል፣ ከብት፣ በግ፣ ፍየል፣ ግመል በጋራ፣ ከብት በጋራ።
(ፈትዋ ለጅነተ ዳኢማህ) (ኢብኑ ዑሠይሚን፡ አሕካሙል ኡድሒያ ወዘካት)
* ከብትና ግመልን በጋራ ማረድ የፈለገ አንዱ ለ7 ሰው ነው መሆን አለበት፡፡
* ፍየልና በግ ለጋራ ማራድ አይቻልም፡፡

3. የሚታረደው እንስሳ እድሜው የደረሰ መሆን አለበት፡፡ በግ 6 ወር፣ ፍየል 1 አመት፣ ከብት 2 አመት፣ ግመል ከሆነ 5 አመት የሞላው መሆን አለበት፡፡

4. የሚታረደው እንስሳ እውር፤ በሽተኛ፤ አንካሳ፤ በጣም ያረጀ፣ አብዛኛው ወይም ግማሽና ከዚያ በላይ የሆነ ጆሮው፣ ጅራቱ፣ ላቱ፣ ቀንዱ፣ የተቆረጠ ወይም የተሰበረ መሆን የለበትም፡፡

5. የሚታረደው እንስሳ ህጋዊ በሆነ መልኩ የራስ ንብረት መሆን አለበት፡፡ (የተሰረቀ፣ የተነጠቀ፣ የተጭበረበረ ..መሆን የለበትም።)

6. የሚታረደው የግድ በተገደበው ጊዜ መሆን አለበት፡፡ እሱም ከዒድ ሶላት በኋላ እስከ ዙልሒጃ 13 ባሉት አራት ቀናት ውስጥ ነው፡፡ ነብዩ ﷺ (ዒድ) ከመሰገዱ በፊት ያረደ በሷ ቦታ (እርዱን) ይድገም፡፡ ያላረደ ይረድ” ይላሉ፡፡ (ቡኻሪ)

7. ያለምንም ልዩነት ከሁለቱም ፆታ ከወንድም ከሴትም ለኡድሒያ ማረድ ይፈቀዳል፡፡ (ኢብኑ ባዝ፣ ፈታዋ ኑሪን ዐለደርብ፡ ካሴት ቁ. 72)

8. ቆዳውንም ይሁን የትኛውንም ክፍሉን መሸጥ አይፈቀድም፡፡ ለአራጁ የሚከፈለውም ከኡድሒያው ቆዳ ወይም ሌላ ክፍሉ መሆን የለበትም፡፡ ነብዩ ﷺ “የኡድሒያውን ቆዳ የሸጠ ኡድሒያ የለውም” ብለዋል፡፡ (ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 2/1055) ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡- “ከኡድሒያው ስጋ፣ ሞራ፣ ቆዳ፣ ወይም ሌላ ነገር መሸረጥ ክልክል ነው፡፡ ምክኒያቱም ለአላህ ያወጣው ገንዘብ ስለሆነ ልክ እንደ ሰደቃ መመለስ አይቻልም፡፡ (ፈታዋ ኢብኒ ዑሠይሚን፡ 25/162) ባይሆን ስጦታ የተሰጠው ሰው ቢሸጥ ምንም ችግር የለበትም፡፡

9. ስጋው ምን ይደረጋል? በእለቱ ከቤት ይበላል፤ ለዘመድ፣ ለጓደኛ፣ ለምስኪን ይሰድቃል ወይም ስጦታ ይሰጣል፣ ቀሪ ከኖረ ያስቀምጣል፡፡ ስጦታ የተሰጠው ሰው ግን መሸጥን ጨምሮ ሐላል በሆነ መልኩ ለፈለገው አገልግሎት ማዋል ይችላል፡፡

10. ኡድሒያውን እራሱ ባለቤቱ ቢያርድ በላጭ ነው፡፡ ካልቻለ ወይም ካልተመቸው ግን ሰው መወከል ይችላል፡፡
ከተለያዩ ፈትዋዎች የተሰበሰበ ነው፡፡

https://t.me/hooral_ayn2
41 views08:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 17:25:37 ወቅታዊ ማስታወሻ ለሙስሊሞች

ውድ ሙስሊም ወንድም ና እህቶች
ይህን ወቅታዊ ማስታወሻዬን ጥቂት ጊዜያችሁን ሰውታቹ እንድታነቡት አደራ አደራ እላለሁ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ አና በጣም አዛኝ በሆነው
ያለንበት ወቅት በ ዱንያ ካሉት ቀናቶች በጣም በላጭ የሆኑ እና አላህ ዘንድ በእነዚህ ቀናቶች የሚሰሩ ስራዎች ከሌሎች በተለየ ና በበለጠ ተወዳጅ የሚሆንበት 10ቱ ቀናት ላይ ነው ያለው

ማስታወሻዬም የሚያተኩረው በእነዚህ ውስጥ በሚገኘው በጣም ታላቅ ና ትሩፋቱ የበዛ ስለሆነው ስለ ዓረፋ
(የዙልሂጃ 9ኛው ቀን) ነው
የአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም የዚህን ቀን ትሩፋቶች በሚገባ አብራርተዋል

ነብያችን እንዲህ ይላሉ : አላህ ሱ.ወ ከዐረፋ ቀን የበለጠ ባሮቹን ከእሳት ነፃ የሚያወጣበት የሆነ አንድም ቀን የለም
ከዛም በመቀጠል ያሉት :እኔም ከኔም በፊት ከነበሩት ነብያት ካሉት ንግግር በላጩ
لا ﺇﻟﻪَ ﺇﻻَّ ﺍﻟﻠَّﻪ ﻭﺣْﺪﻩُ ﻻَ ﺷَﺮِﻳﻚَ ﻟﻪُ، ﻟَﻪُ ﺍﻟﻤُﻠْﻚُ، ﻭﻟَﻪُ ﺍﻟﺤﻤْﺪُ، ﻭَﻫُﻮ ﻋَﻠَﻰ ﻛُﻞِّ
ﺷَﻲﺀٍ ﻗَﺪِﻳﺮ
ላ ኢላሃ ኢሏሁ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ አላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር የሚለው ነው::
ይህን ዚክር በብዛት በማለት እንበርታ
ሌላው ነብያችን እንዲህ ብለዋል
በላጬ ዱዓ ማለት የዓረፋ ቀን የሚደረግ ዱዓ ነው

በዚህ በላጭ በሆነው የዓረፋ(ዙልሂጃ 9) ቀን አላህ ሱ.ወ
-ከእሳት ነፃ ከሚያደርጋቸው
-ወንጀላቸው ከሚማርላቸው ባሮቹ መሆን የፈለገ ሰው
የዓረፋን ቀን ይፁም
ነብያችን እንዲህ ይላሉ :
{የዐረፋ ቀን በመፆም አላህ ያለፈውንና የሚመጣውን አመት ወንጀል እንደ ሚምር እተሳሰባለሁ}
{የዐረፋ ቀን የፆመ የሆነ ሰው ተከታታይ የሆኑ የሁለት አመት ወንጀሎቹን ይማርለታል}
የተውሂድ ቃል ዚክር ማለትን ያብዛ
ላ ኢላሃ ኢሏሁ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ አላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር
አላህ እንዲምረው እና ከእሳት ነፃ ከሚሆነው እንዲያደርገው መለመንን ያብዛ
አሏሁመ አእቲቅ ሪቃበና ሚነን ናር የምትለዋን ዱዓ በማለት አላህን እንለምን
በዚህ ቀን ዱኣ ተቀባይ መሆኑ በጣም የሚከጀልበት ነው
ለዚህም ቀን ኸይር ፈላጊ የሆነ
ሙስሊም ራሱን ባለቤቱን እህት ወንድሞቹንና ልጆቹን ይህንን የተከበረ ቀን እንዲፆሙ ይቀሰቅሳል
አላህ ሱ.ወ የዚህን ቀን ትሩፋቶች ከሚያገኙ እና ወንጀላቸው ከሚማርላቸው ሰዎች እንዲያደርገን እለምነዋለሁ በመልካም ዱዓቹ አትርሱኝ

ይህን አንገብጋቢ ማስታወሻ ለምታውቁትም ለማታውቁትም ሙስሊም ለሆነ አካል እንድታሰራጬ እና የመልካም ስራ ተቋዳሽ እንድትሆኑ እጠይቃለሁ
ወሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ
طلحة أحمد
40 views14:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 15:24:06 ቁርአን የልብ ብርሃን

➧ከቁርአን ጋር እንኑር
53 views12:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 07:03:23 አላሁ አክበር አላሁ አክበር አላሁ አክበር
ላ ኢላሃ ኢለላህ
አላሁ አክበር አላሁ አክበር
ወሊላሂል ሐምድ

ማራኪ የሆነ ተክቢራ ነው

በድምፃችሁ ባትሉ እንኳ
በቤታችሁ፣
በሱቃችሁ፣
በመኪናችሁ ስትሆኑ በእስፒከር በትልቁ ክፈቱና ቢያንስ ድባቡን አድምቁት


https://t.me/+sgRX_ZvXO5dlOGM8
56 views04:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 14:58:45 عن أبي قتادة الأنصاريِّ رضي الله عنه أن النبي صلى الله عليه وسلم قال:

[ صِيَامُ يَوْمِ عَرَفَةَ أَحْتَسِبُ عَلَى الله أَنْ يُكَفِّرَ السَّنَةَ الَّتِي قَبْلهُ وَالسَّنَةَ الَّتِي بَعْدَهُ ]

رواه مسلم


«::::::::::::::::» «:::::::::::::::»

ከአቢ-ቀታዳ አል-አንሷሪ(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተወራው ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:-

[ የዐረፋን ቀን መጾም ከሱ በፊት (ያለፈውን) አመት እና ከሱ ቡሃላ(የሚቀጥለውን) አመት ወንጀል ያስሰርዛል ብዬ ከአሏህ እከጅላለሁ። ]

ሙስሊም ዘግበውታል።
82 views11:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 07:52:33 ሐበሻው ቢላል ኢብኑ ረበሕ
(ረዲየሏሁ ዐንሁ)
┈┈•••✿❒ ❒✿•••┈┈

ክፍል
❒❒ ❒❒


ቢላል ረዲየሏሁ ዐንሁ ግን ለኢስላም ብቻ ሳይሆን ለመላው የሰው ዘር የሚያኮራአቋም ከመውሰድ ወደ ኋላ አላለም። አላህ ሱብሐነሁ ወተዓላ የአንድ ሰው የቆዳ ቀለሙ መጥቆር ከፍተኛውን የኢማን ደረጃ ከማግኘት የሚያግድ እንደማይሆን በቢላል ረ.ዐ ተምሳሌት አስተምሯል። ቢላል ለዘመኑ ሰወችና ከእርሱ በኋላ ለመጣው ትውልድ እንዲሁ ም እምነት ለሚያጋሩትም ይሁን ለማያጋሩት ወገኖች ያስተማረው ትምህርት ቢኖር የህሊና ነፃነትና ሉዐላዊነት ምድርን የሞላ ንዋይም ሆነ አሰቃቂ ቅጣት ሊበግረው እንደማይችል ነው።

ቢላር ረዲየሏሁ ዐንሁ እርቃኑን በትኩስና አሸዋማ መሬት ላይ እንዲተኛና ቋጥኝ ድንጋይ ደረቱ ላይም እንዲጫን ተደርጓል። ግን እምነቱን ሊቀይር አልፈቀደም። በተከታታይ እና በተደጋጋሚ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ተፈፅሞበታል። የቁረይሽ ሹማምንት አንድን ባርያ ሊያ ሳምኑና ወደ ቀድሞው እምነቱ ሊመልሱት ባለመቻላቸው ቁጭትና ሀፍረት ስለ ተሰማቸው ክብራቸውን ለመጠበቅ ሲሉ ቢላል ቢያንስ ቢያንስ ስለ አማልክቶቹ ጥቂት በጎ ነገር እንዲናገር ጠይቀውት አሻፈረኝ አለ።.

•••✿❒ ❒✿•••

ህይወቱን ቀስቃይ ምናልባትም ከሞት ለማዳን አማልክታቸውን ከልቡ እንኳ ባይሆን ማመስገን በቂ ነበር።ታላቁ ቢላል ረዲየሏሁ ዐንሁ ግን ከስጋዊ ህመም መንፈሳዊ የበላይነትን በመምረጡ ለጠላቶቹ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ፍቃደኛ አልሆነም። ይልቁንም በተደጋጋሚ፦ "አሐድ....አሐድ..." በማለት የመለኮትን አንድነት ያውጅ ነበር።

"ላት" እና "ዑዝዛ" የተሰኙ ጣዖታትን እንዲያወሳ ያለ መታከት ይጠይቁታል። መልሱ ግን "አሐድ....አሐድ" ነበር። እኛ የምንለውን ደግመህ በል በማለት ይገርፉታል። በምፀታዊ ቃልም፦ እናንተ የምትሉትን ለመናገር ምላሴ አይችልም... ይላቸዋል። "ላት" እና "ዑዝዛ" ጌታዎች ናቸው ካልክ አንተንም እምነትህንም እንተዋችኋለን፣ በእርግጥ እኛ ራሳችን ስቃይ ተቀባዪች የሆንን ይመስል አንተን በማሰቃየት ደክመናል።" ፅንቅላቱን በመነቅነቅ "አሐድ...አሐድ" የሚል ምላሽ ከመስጠት ባሻገር እጅ አልሰጠም ቢላል ረዲየሏሁ ዐንሁ።

•••✿❒ ❒✿•••

ቁረይሾች ተስፋ አልቆረጡም እናሰቃየው፥ እርሱ የኛ ወገን ነው። እናቱም የኛ አገልጋይ ነች። በመስለሙ እኛን የቁረይሽ መዛበቻ አያደርገንም። ቢላል ግን ለተንኮላቸው አልተንበረከከም ፦አሐድ.....አሐድ....." በማለት የ አላህን አሐዳዊነት ገለፀላቸው። ቁረይሾች ቢላል ነብሱን እስኪስት ድረስ ደበደቡት።

አቡበክር ረዲየሏሁ ዐንሁ ቢላል ረዲየሏሁ ዐንሁ ከሚሰቃይበት ቦታ ደረሱ ደብዳቢወችንም ወቀሷቸው፦"አንድ ሰው አምላኬ አላህ ነው! በማለቱ ብቻ ልትገድሉት ትሻላችሁን? ከዚያም ኡመያ ኢብን ኸለፍን፦ ቢላልን ከገዛህበት ዋጋ ጨምሬ እከፍልሀለው። ልቀቀው አሉት።

•••✿❒ ❒✿•••

ኡመያ በቢላል (ረዲየሏሁ ዐንሁ) ተስፋ ስለቆረጠ ከሚገድለው ገንዘብ ቢያገኝበት የተሻለ መሆኑ ተሰማው፣ በአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) ጥያቄ ከልብ ተደስቷል። አቡበክር ረዲየሏሁ ዐንሁ ቢላልን ከገዙት በኋላ ነፃነቱን አወጁለት። አቡበክር ሲዲቅ ረዲየሏሁ ዐንሁ ቢላል ረዲየሏሁ ዐንሁን ተረክበው ሊሆዱ ሲሉ ኡመይያ እንዲህ በማለት ተሳለቀ፦ "በላትና ዑዝዛ ምላለሁ በአንድ ወቄት ወርቅ ካልሆነ አልገዛህም ብትለኝ እንኳን እሸጥልህ ነበር!" አቡበክርም (ረዲየሏሁ ዐንሁ)፦ "በአላህ ስም እምላለሁ! በመቶ ወቄት ወርቅ ካልሆነ አልሸጥልህም ብትለኝ ኖሮ የጠየቅከውን እክፍልህ ነበር።" አሉት።

አቡበክር ቢላልን (ረዲየሏሁ ዐንሁም) ወደ መልእክተኛው ﷺ በመውሰድ ነፃ መውጣቱን አበሰሩዋቸው ትልቅ ደስታ ሆነ። ነብዩ ሙሀመድ ﷺ ወደ መዲና ከተሰደዱ በኋላ "አዛን" ማሰማት አስፈላጊ ሆኖ በተገኘበት ወቅት ይህን ተግባር እንዲፈፅም አንድ ሰው መምረጥ ግድ ሆነ። የዘር አድሎ የማያውቀው ኢስላም ቢላል ረዲየሏሁ ዐንሁ ን በ "ሙአዚን"ነት መረጠ።

•••✿❒ ❒✿•••

በሙስሊሞች እና በቁረይሾች የነበርው ቅራኔ ወደ ወታደራዊ ፍጥጫ ተቀየረ። የቁረይሽ ሰራዊት ወደ መዲና ተመመ። በርካታ የቁረይሽ ሹማምንትም በጦርነቱ ተሳታፊ ለመሆን በሙሉ ልብ ተነስተዋል። ቢላል ረዲየሏሁ ዐንሁ ላይ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ሲፈፅም የነበረው ኡመያ ኢብን ኸለፍ ግን ከሀገሩ ለመውጣት ባለመፈለጉ ምክንያት ፈጥሮ ለመቅረት አስቦ ነበር።

ጓደኛውና በቢላል ረዲየሏሁ ዐንሁ ላይ እኩይ ድርጊት እንዲፈፅም ሲያበረታታው የነበርው ዑቅበት ኢብን አቢ ሙዓይጥ የኡመያን በጦርነቱ ተሳታፊ ያለመሆን ሰማ። ሴቶች ጭስ የሚሞቁበት ሸክላ በመውሰድም ወዳጆቹ በተሰበሰቡበት እንዲህ አለው፦ "የዐሊይ አባት ሆይ! በዚህ ሸክላ ጪስ ሙቅበት፥ አንተ ሴት ነህ አለው።

ኡመያ የሀፍረት ማቅ መልበሱ ስለተሰማው፦ አንተንም ሆነ ይዘህ የመጣኸውን ነገር ፈጣሪ ያጥፋችሁ..." በማለት ብስጭቱን ከገለፀ በኋላ ወደ ጦር ሜዳ ለመዝመት ዝግጅት ጀመረ። ክስተቱ አስገራሚ ነው። ዑቅበት ኢብን አቢ ሙአይጥ በቢላል ረዲየሏሁ ዐንሁ እና ወገን ዘመድ በሌላቸው ሙስሊሞች ላይ ጥቃት እንዲፈፀም የሚያበረታታ ሰው ነበር። ዛሬ ኡመያ ኢብን ኸለፍን ወደ በድር ጦርነት እንዲሄድ አስገድዶታል።

•••✿❒ ❒✿•••

ምንአልባትም የሁለቱም የህይወት ፍፃሜ ቀርቦ ይሆናል።
ውጊያው ተጀመረ። ሙስሊሞች "አሏሁ አክበር....አሐድ....አሐድ..." ሲሉ ይሰማል ኡመያ ይህን ቃል በሚገባ ያስታውሰዋል. ትናንት የቢላል ረዲየሏሁ ዐንሁ የጣር ድምፅ ነበር። አሁን ደግሞ የአዲሱ ትውልድ መፈክር ሁኗል። ልቡ ተሸበረ

•••✿❒ ❒✿•••

የተለያዩ ጣፋጭ አስተማሪና ኢስላማዊ
ታሪኮች የሚቀርቡበት ምርጥ ቻናል ነው።

•════••• •••════•
ሼር JoiN & Share
https://t.me/AAASELEFYA
https://t.me/AAASELEFYA
61 views04:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 08:51:50 ❒ ሐበሻው ቢላል ኢብኑ ረባሕ ረዲየሏሁ ዐንሁ
┈┈•••✿❒ ❒✿•••┈┈

ክፍል
❒❒ ❒❒

የአቡበክር (ረ.ዐ) ስም ሲነሳ ዑመር ኢብኑል ኸጧብ (ረ.ዐ) እንዲህ ይሉ ነበር፦

«አቡበክር ልዑላችን ነው። የኛን ልዑልም ነፃ አውጥቶልናል።»

ዑመር ረ.ዐ "ልዑላችን" ሲሉ ያሞካሹት ግለሰብ ታላቅ ሰው ነበር። እጅግ በጣም ዕድለኛ። ይህ ሰው እንዲህ አይነቱን የሙገሳ ቃል ሲሰማ ግንባሩን ደፋ፥ ዐይኑን ገርበብ በማድረግ "እኔ ትናንት ባርያ የነበርኩ የሀባሻ ሰው ነኝ" ይል ነበር። ለመሆኑ የትላንቱ የሀበሻ ባሪያ የዛሬው ልዑል ማን ይሆን ?

ቢላል ኢብኑ ረባሕ ነው። የኢስላም ሙአዚን እና የጣዖታት አሳፋሪ ሰው ነው። የእምነትና የእውነተኝነት (ኢማንና ሲድቅ) ወርቃማ ፍሬ ነው። በየትኛውም ጊዜና ቦታ ከሚገኙ ሙስሊሞች መካከል ቢያንስ ከአስር ሰባቱ ቢላልን ያውቁታል። ስሙን ዝናውን እና ሚናውን በሚገባ ያወሱታል።

•••✿❒ ❒✿•••

በሚሊዬን የሚቆጠሩ ሰወች አቡበክርንና ዑመርን (ረ.ዐ) እንደሚያውቁ ሁሉ የቢላልም ረ.ዐ ስም እንግዳ አይሆንባቸውም። ሕፃናትን ቢላል ማን ነው ብለህ ብትጠይቅ የረሱል ﷺ "ሙአዚን" ነው ይሉሀል። አሳዳሪው በ ጋለ ድንጋይ ላይ በማስተኛት ሲያሰቃየው ወደ ጥንት እምነቱ ከመመለስ ይልቅ "አሐድ...አሐድ... በማለት ፅናቱን የገለፀ ሰው ነበር የሚል ምላሽ ታገኛለህ።

•••✿❒ ❒✿•••

ይህ ሁሉ ታላቅ ዝናና እውቅናን ያተረፈው ቢላል ኢስላምን ከመቀበሉ በፊት በሕዝቡ ዘንድ ከእንስሳ ተለይቶ የማይታይ እና የተናቀ ባርያ መሆኑን ማስታወስ ያሻል። ቢላል ረ.ዐ ኢስላምን ባይቀበል ኖሮ የአሳዳሪውን ግመል ከመጠበቅ ሌላ የህይወት ሚና የሌለው፣ እንኳን ከሞተ በኋላ በሕይወት ዘመኑም አስታዋሽ የሌለው ሰው ሆኖ በቀረ ነበር።

ነገር ግን በእውነተኛ ኢማን በመታነፁ ፣ ታታሪና ቀና በመሆኑ የገባበትም ሀይማኖት እጅግ ታላቅ በመሆኑ ቢላል ረዲየሏሁ ዐንሁ ኢስላም ከሚያወሳቸው ድንቅ ሰወች መካከል በመጀመሪያው ምዕራፍ ተጠቃሽ ለመሆን በቅቷል። እንዲሁም ከፍተኛ የታሪክ ሰወች የቢላልን ያህል ትውስታ አልተቸሩም።

•••✿❒ ❒✿•••

የቆዳው መጥቆር፥ የሙያውና የዘሩ እውቅ ያለመሆን፥ በሰወች ዘንድም ትናንት ነፃ የወጣ ባርያ መሆኑ ቢታወቅም ኢስላምን ከመረጠ በኋላም ወደ ከፍተኛ ደረጃና ማዕረግ ለመሸጋገር አላገደውም። እንደ ቢላል ዐረባዊ ያልሆነ ባርያ ዘመድና ኋይል የሌለው ሰው ለታላቅ እጣ ይበቃል ብሎ የሚገምት አልነበረም።

ከቁረይሽ ነገድ ውስጥ በታላቅነታቸው የሚታወቁና ኢስላምን የተቀበሉ ግለሰቦች ሲመኙት የነበረውን የረሱል ﷺ "ሙአዚን" የመሆን እድልም ቢላል ረዲየሏሁ ዐንሁ ማግኘቱ የሚደነቅ ነው።
ወደ ዋናው ታሪኩ እንግባ የቢላል እናት ጥቁር ሀበሻ ናት። የአላህ ውሳኔ ሆነና የበኒ ሹምህ ጎሣ አባል ለሆነ ሰው በባርነት ተመዘገበ። እናቱም የዚሁ ጎሳ ባርያ ነበረች።

•••✿❒ ❒✿•••

የቢላል ረ.ዐ እናት ጥቁር ሀበሻ ናት። የአላህ ውሳኔ ሆነና የበኒ ሹምህ ጎሣ አባል ለሆነ ሰው በባርነት ተመዘገበ። እናቱም የዚሁ ጎሳ ባርያ ነበረች። ዛሬ አንዳች መብት የሌለውና ለነገም አንዳች ተስፋ ያሌለው ተራ ባርያ ነበር-ቢላል ረ.ዐ ።

የሙሀመድ ﷺ ዜና ከቢላል ጆሮ መግባት ጀመረ። የመካ ሰወች በትኩስ ወሬነት የሚነጋገሩት ሙሀመድ ﷺ ነብይ ነኝ ብሎ የመነሳቱን ጉዳይ ነበር። አሳዳሪውና እንግዶቹም በዚሁ ርዕስ ጉዳይ ላይ ሲወያዩ ይሰማል። በተለይ ኡመያ ኢብኑ ኸልፍ የተባለው አሳዳሪው ተንኮል የተሞላበት ውይይትና ምክክር ከጥቂት ሰወችና ከበርካታ እንግዶች ጋር ሲነጋገር አድምጦታል።

•••✿❒ ❒✿•••

የቢላል ጆሮ ተሰብሳቢወቹ ከሚናገሩት የጥላቻ ንግግር ውስጥ ሙሀመድ ﷺ ስለተነሱበት አላማና ምን እያሉም እንደሚያስተምሩ ሊቀነጭብ ቻለ ። አዲስ የመጣው ዲን ለአካባቢው እንግዳና ስር ነቀል ለውጥ ለማምጣት ያለመ ሙሀመድም ﷺ ምንም እንኳ ነብይ ነኝ ብለው በመናገራቸው ተቃውሞ የገጠማቸው ቢሆንም ታማኝ፥ እውነተኛና በጥሩ ሥነ-ምግባር የታነፁ መሆናቸውን ከጠላቶቻቸው ቁንጮወች አንደበት አድምጧል።

ሙሀመድ አንድም ቀን ዋሽቶ አያውቅም። ዝምተኛም ሆነ እብድ አልነበረም።...ዛሬ ግን እኛ እርሱን በነኝህ ነገሮች መጥራት ይኖርብናል-ወደርሱ የሚጎርፉትን ሰወች መግታት የምንችለው በዚህ መንገድ ነው" በማለት ሲዶልቱ ሰምቷቸዋል። ሙሀመድን ﷺ የሚቃወሙት በቅድሚያ የአባቶቻቸውን ዲን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ሲሆን። በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ የቁረይሽን የበላይነት የሚያከስም መሆኑ ስለ ተሰማቸው ነው።

•••✿❒ ❒✿•••

ቁረይሽ በመላው ዐረብ ለጣዖታዊው እምነት ማዕከል በሆነችው መካ የሚገኝ ነገድ በመሆኑ ተፈሪነቱና ከበሬታው የላቀ ነበር። በሶስተኛ ደረጃ በኒ ሀሺም ተብሎ በሚታወቀው የነብዩ ሙሀመድ ﷺ የዘር ሀረግ ቤተሰብ ላይ ያሳደሩት ቅናትና ምቀኝነት ነበር። ከበኒ ሐሺም ቤተሰብ ነብይና መልእክተኛ መምጣቱን እንደ ሽንፈት ቆጥረውታል። ሁሉም ቤተሰብና ጎሳ ነቢይ ከራሱ ወገን እንዲመጣ ይሻ ነበር።

ከእለታት አንድ ቀን ቢላል ኢብኑ ረባሕ ረዲየሏሁ ዐንሁ የኢማን ብርሀን ፈነጠቀበት። ምርጭልውን ይፋ ማድረግ እንዳለበት ወሰነ። ወደ ረሱል ﷺ በመሄድም ለኢስላም እጁን መስጠቱን ይፋ አደረገ። የቢላል መስለም በመካ ምድር ተሰማ። የበኒ ጀመህ መሪወች በቁጣ ተወጣጠሩ። በተለይ አሳዳሪው የኢስላም ጠላት ኡመያ ኢብን ኸለፍ ሀበሻዊው ባሪያው መስለሙ እንደታላቅ ነውርና ንቀት ቆጥሮታል።

ከዛም እንዲህ አለ "ይህ ኮብላይ ባሪያ በመስለሙ ፀሀይ ተመልሳ የምትጠልቅ አይመስለኝም.." ሲል ቁጭቱን ገለፀ። ቢላል ረዲየሏሁ ዐንሁ ግን ለኢስላም ብቻ ሳይሆን ለመላው የሰው ዘር የሚያኮራአቋም ከመውሰድ ወደ ኋላ አላለም። አላህ ሱብሐነሁ ወተዓላ የአንድ ሰው የቆዳ ቀለሙ መጥቆር ሳይሆን የሚመለከተው የልብን ንፅና ነው።

#ኢንሻአላህ #ይቀጥላል

•••✿❒ ❒✿•••

የተለያዩ ጣፋጭ አስተማሪና ኢስላማዊ
ታሪኮች የሚቀርቡበት ምርጥ ቻናል ነው።

•════••• •••════•
ሼር JoiN & Share
https://t.me/AAASELEFYA
https://t.me/AAASELEFYA
67 views05:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ