2022-07-07 22:23:06
" #የነገንአውቃለሁ "
ባይ ዘንድ መሄድ እና መጠየቅ በኢስላም ፍርዱ ምንድን ነው?
ወደ ጠንቋይ ቤት የሚሄድ ሰው ለሦስት ይከፈላሉ፦
•••━══❁✿❁══━•••
➮የመጀመሪው ክፍል ፦
ወደ ጠንቋይ ቤት በመሄድ ስለአንዳች ነገር ጠይቆ ነገር ግን #አያምንበትም (ያለውን አይቀበለውም) ይህ ተግባር ሐራም ይሆናል።
ይህን ያደረገ ደግሞ ቅጣቱ የአርባ ቀን ሰላቱ ተቀባይነት አያገኝም። በሙስሊም ዘገባ ፀድቆ እንደመጣው የአላህ መልክተኛ እንዲህ ብለዋል ፦
“ጠንቋይ ጋር መጥቶ የጠየቀ የአርባ ቀን ወይም የአርባ ለሊት ሰላት ተቀባይነት አያገኝም።”
•••━══❁✿❁══━•••
➮ሁለተኛው ክፍል ደግሞ ፦
ጠንቁይ ቤት መጥቶ ከጠየቀ በኋላ የተናገረውን #አምኖይቀበለዋል። ይህ በአላህ መካድ (ኩፍር) ነው። ምክንያቱም የሩቅ ምስጥርን አውቃለሁ ብሎ የሚሞግትን እውነት ነው ብሎ መቀበል ቀጣዩን የአላህን አንቀፅ እንደማስተባበል ይቆጠራል።
«በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ ሩቅን ምስጢር አያውቅም፡፡ ግን አላህ (ያውቀዋል)፡፡ መቼ እንደሚቀሰቀሱም አያውቁም» በላቸው፡፡” [አነምል:65]
ለዚህም ሲባል በሰሒህ ሐዲስ ከመለክተኛው እንዲህ የሚል መልክት መጥቷል፦
“ጠንቋይ ጋር በመምጣት ያለውን አምኖ የተቀበለ በሙሐመድ የወረደውን (ቁርኣን) አስተባብሏል።”
•••━══❁✿❁══━•••
➮ሦስተኛው ክፍል ደግሞ ፦
ወደ ጠንቋይ በመምጣት ሰዎች (የጠንቋይ) ማንነቱን እንዲረዱ እና ጠንቋይ መሆኑን ፤ሰዎች ላይ በማመሳሰል እንደሚያሳስትና እንደሚያጠም ለሰዎች ያጋልጥ ዘንድ የእውቀት ባለቤት የሆነ ሰው አንዳንድ ጥያቄዎች ቢያቀርብ ችግር የለውም።
ለዚህም ማስረጃው ነቢዩ ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም ኢብኑ ሰያድ ዘንድ በመምጣት ወይም ነቢዩ (ሰለለሁ አለይሂ ወሰለም) ኢብኑ ሰያድ ጋር ሄደው በውስጤ ምን ደብቄለሁ? ብለው ጠየቁት። እሱም፦ “ጭስ” አለ ነቢዩም (ሰለለሁ አለይሂ ወሰለም)፦ ዝም በል! ወሰንህን ልታልፍ አትችልም።” እንዳሉት ተገኝቷል። ሌላም መረጃ ማቅረብ ይቻላል ።
ውድ አንባቢያን ሆይ ! አያሌ ሰዎች በማዎቅም ሆነ ባለ ማዎቅ እነዚህ ሰዎች ዘንድ ብዙዎቹ በድብቅ አንዳዶቹ በግልጽ የሚጓዙ እጂግ ቁጥራቸው የበዙ ናቸው ።
ያውም የምናውቃቸው ቤተሰቦቻችን ፣ ጎረቤቶቻችን ፣ የመንደራችን ፣ የሃገራችን ሰዎች ናቸው።
ስለሆነም ሰዎችን የድግምትን አስከፊነት ባገኘነው እድል ሁሉ ማስተዋዎቅ የግድ ይኖርብናል።
አላህ ይመልሳቸው !አላህ ይጠብቀን
ጌታ ጋር ተጣልቶ ጠንቋይ ከማመን!
SHARE FORWARD
╔══════════════
JOIN: @IQRATV_official
JOIN: @IQRATV_official
╚══════════════
12 views🇲 🇦 🇲 🇮 🇱 🇦, 19:23