2022-07-13 22:48:25
ዕብራውያን 3፥12 ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እግዚአብሔርን በመካድ ወደ አለማዊነትና ህይወት ወደሌለበት ወደ አሮጊቶች ተረት ዘወር ማለት በአማኞች ዘንድ እየተለመደ የመጣ ነገር ሆኗል
ይህ ሁኔታ ታዲያ በቅዱሳን መካከል ግራ መጋባትን የሚፈጥርና ልብን የሚያሳዝን ዜና ሆኖ ብዙ ጊዜ አልፏል
በአካል ውስጥ የአንድ ብልት ህመም ለሌሎች እየተረፈ ፤ ዘላለም አብሮ ላለመቀጠል ከአካሉ ተሰብሮ የሚወድቀው ክፍል ደግሞ እጅጉን እያስመረረ ለቤተክርስቲያን የበረታ ሀዘን ነው
በሮሜ መጽሐፍ እንዳየነው ታዲያ ከግንዱ ተቆርጦ የወደቀው ቅርንጫፍ መልሶ ግንዱ ውስጥ ሊገባና ሊጣበቅ አሁንም በእግዚአብሔር ዘንድ ለወደቀው ለዚያ ብልት ተስፋ አለው(ሮሜ 11፥23-24)
ነገር ግን ለትምህርታች እንዲሆን የወደቁ ብዙዎች ከሚደረድሩት ምክንያት ባሻገር በትክክል ሰዎችን ከእግዚአብሔር ሊለይና እግዚአብሔርን ሊያስክድ ስለሚችል ዋና ነገር ከመጽሐፍ እንመልከት
ሐዋርያው ጳውሎስ በአንድ ስፍራ "ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ፥ ወይስ ጭንቀት፥ ወይስ ስደት፥ ወይስ ራብ፥ ወይስ ራቁትነት፥ ወይስ ፍርሃት፥ ወይስ ሰይፍ ነውን? ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን፥ እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው። በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን። ሞት ቢሆን፥ ሕይወትም ቢሆን፥ መላእክትም ቢሆኑ፥ ግዛትም ቢሆን፥ ያለውም ቢሆን፥ የሚመጣውም ቢሆን፥ ኃይላትም ቢሆኑ፥ ከፍታም ቢሆን፥ ዝቅታም ቢሆን፥ ልዩ ፍጥረትም ቢሆን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን ካለ ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን እንዳይችል ተረድቼአለሁ።"በማለት እጅግ ብዙ ኃይላትን ሲዘረዝርና እነዚህ ኃይላት ሁሉ ግን በክርስቶስ ካለን ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለዩን የማይችሉ እንደሆኑ ያመለከታል(ሮሜ 8፥35-39)
ሐዋርያው የዘረዘራቸው እነዚህን ኃይላት በባህሪያቸው ከውጭ ተጽዕኖ የሚመነጩ በመሆናቸው
ውጫዊ ኃይላት ብለን ልንላቸው እንችላለን
የትኛውም ውጫዊ ኃይል አማኞችን በክርስቶስ ካለ ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለይ የሚችል አይደለም
ይኸው የእግዚአብሔር ሰው ሐዋርያው ጳውሎስ ታዲያ በዕብራውያን መልዕክቱ ላይ እግዚአብሔርን አስክዶ ከእርሱ ፍቅር ሊለየን ስለሚችል አንዳች ኃይል ግን እንዲህ ይጠቁማል
“ወንድሞች ሆይ፥ ምናልባት ሕያው እግዚአብሔርን የሚያስክዳችሁ ክፉና የማያምን ልብ ከእናንተ በአንዳችሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ” ዕብ 3፥12
ክፉና የማያምን ልብክፉና የማያምን ልብ እግዚአብሔርን ወደ መካድ ውድቀት ሊያመጡ የሚችሉ
ውስጣዊ ኃይላት ናቸው
በክፋት የተሞላ ልብ ለእግዚአብሔር ፍቅር መቀመጫ ሊሆን አይችልም
የማያምን ልብም እንዲሁ የእግዚአብሔርን ልጅ ክርስቶስ ኢየሱስን በውስጡ ለማስቀመጥ አይቻለውም
“በመንፈሱ በውስጥ ሰውነታችሁ በኃይል እንድትጠነክሩ ክርስቶስም በልባችሁ በእምነት እንዲኖር...” ኤፌ 3፥16-17
እንግዲህ እኛ አማኞች ሁልጊዜ ልባችንን ከእነኚህ ብንጠነቀቅ ከክህደት እናመልጣለን እንዲህ እንደተጻፈ:-
“አጥብቀህ ልብህን ጠብቅ፥ የሕይወት መውጫ ከእርሱ ነውና።” ምሳሌ 4፥23
@intoglory
273 views𝖋𝖙.𝖕𝖆𝖚𝖑, 19:48