1444ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተከብሯል። የዩኒቨርሲቲው አመራሮች እና | Injibara University
1444ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተከብሯል።
የዩኒቨርሲቲው አመራሮች እና የእስልምና ሐይማኖት ተከታይ ተማሪዎች 1444ኛው የኢድ አልፈጥር በዓልን በጋራ አክብረዋል።
የኢድ አልፈጥርን በዓል በማስመልከት የተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በላይ ዘለቀ (ዶ/ር) እና ሌሎችም አመራሮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የተማሪ ህብረት አባላት እና በጸጥታ ሥራ ላይ ተሠማርተው የሚገኙ የፌደራል ፖሊስ አባላት በዓሉን በጋራ አክብረዋል።
ኢድ ሙባረክ!
ሚያዚያ 13/2015 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ