እስቲ ፈገግ በሉልኝ አንድ ሰው በሚስቱ ክፋት ተማረረና ለአንድ ሸህ ብሦቱን ተናገረ፡፡ እነ ሸህ “ምላሷን አልቻልኩም፣ አቆሰለችኝ፡፡” አላቸው፡፡ ሸሁም “እስቲ አትናገራት፤ መጥፎ ይሁን ጥሩ በምትሠራው ነገር ሁሉ ዝም ብለህ አወድሳት፡፡” አሉት። ሰውዬውም የሸሁን ምክር ተቀበለ፡፡ ወደ ተግባር ለመለወጥም ተዘጋጀ፡፡ አንድ ቀን ሚስቱ እራት አመጣችለት፡፡ አስቀምጣለትም ዘወር አለች፤ እንዳትርቅበት እየተጣደፈ ገና አንድ እንደጎረሰላት “ዉይ ዉዴ የዛሬው ምግብሽ ሲጣፍጥ እኮ!” አላት፡፡ እሷም “አልቀረብህም፤ እንደው እኮ ትገርማለህ! ስንት ዓመት ሙሉ መርዝ የበላህ የኖርክ መሰለህ፤? እኔ የሠራሁትን ምግብ አንድም ቀን ሳታሞግስና ሳታደንቅ ዛሬ ጎረቤታችን ያመጣችዉን ምግብ የምታደንቀው?፡፡ ለካስ የቀረበለት ምግብ ከጎረቤት የመጣ በሀዲያ መልክ የመጣ መሆኑን አላወቀም ነበር ሚስኪን ባል ወይ ኪሳራ። . . #Ⓔ︎Ⓛ︎Ⓤ︎ነኝ ᴊᴏɪɴ & sʜᴀʀᴇ @ikhlasstudents @ikhlasstudents 9.9K views Elham , 17:20