2022-08-28 20:54:06
ፍቅር የመሰለ
ክፍል ሰባት (የመጨረሻው ክፍል)
(ሪና ሁዳ)
መንገድ ላይ ጥንድ ጥንድ ሆነው ዎክ እያረጉ ፋፊ <ኹሉዴ....> አላት።
<ወዬ ፋፊ>
<ኹሉዴ... አንድ የምነግርሽ ነገር አለኝ... ከዚህ በላይ እንድትጎጂብኝ አልፈልግም..> አላት። አሁን ግራ ተጋባች።
<እሺ ምንድን ነው?> አለችው።
<ያቺ....... እኔ የምወዳት.. እሱዋም የምትወደኝ፤ ግን መናገር የፈራችውን ሴት እውነታ.... ልነግርሽ እፈልጋለሁ!> አላት። ኦኬ ጊዜው ደረሰ ማለት ነው? አለች በሆዷ
<ማን ናት?> አለችው። ፋፊ ትንሽ ልቧን ካንጠለጠለው በኋላ <ክርስቲና... > አላት። ኹሉድ ደንግጣለች። ቃል ማውጣት ተስኗት ዝም ብላ የሚያወራውን ታዳምጠዋለች።
<ኹሉዴ... ክርስቲን እወዳታለሁ። ቤቷ ስሄድ ሁሌ ምልክት ትሰጠኛለች ግን ደፍራ መናገር አልቻለችም። ደግሞ በእኔና በአንቺ መካከል ያለውንም ሁሉንም ታሪክ ታውቃለች።.....>
<ለምን ለኔ መንገር አስፈለገ?> አለችው ቆጣ ብላ።
<ኹሉዴ እንደወደድሺኝ እንኳን እኔ ማንኛውም ሰው ከአይንሽ መረዳት ይችላል። አሁን መናደድሽም አንዱ ምልክት ነው። ግን እንድትጎጂ ስለማልፈልግ ብቻ እንደነገርኩሽ እወቂልኝ....> አላት። ምን ትበል? አንዲት ቃል ሳትተነፍስ ቤቷ ደረሰች። ቻው እንኳን አላለችውም ነበር። ቤቷ ከገባች በኋላ አልቅሳ ሲወጣላት ለሰባህ ነገረቻት። ሰባህ ከመናደዷ የተነሳ ደውላ ልትሰድበው ሁላ አቃጥቷት ነበር። ካልወደዳት ለምን እንድትወደው አደረገ? ጨዋታ ላይ ነበር እንዴ?
*
ጊዜው ነጎደ። ሰባህም ወደ ክፍለ ሀገር ተመለሰች ፉዓዶችም ወደ ጊቢ አቀኑ። ኹሉድ ግን የክርስቲና ጉዳይ እስካሁን ውስጧን ይሰረስራታል። ለምን እንደደበቀቻትም ብቻ ሳይሆን ይህን ያህል ጊዜ እያወቀች እንዴት እንደተወቻት ማወቅ ፈልጋለች። አንድ ቀን ሆነ ብላ በጠዋት ቤቷ ትሄዳለች። ሀሳቧ የነበረው ጠይቃት ለመመለስ ነበር። ቤት ከሄደች በኋላ ግን ፈራች። እንዴት ትንገራት? ስለ ፉዓድ አንድም ሳታወራ ምሳ ሰዓት ደረሰ። ምሳ ከበሉ በኋላ እነ ክርስቲ ሱቅ ገብተው ቁጭ እንዳሉ ደፍራ ለመናገር ወሰነች።
<ፉዓድ ምንሽ ነው?> አለቻት ቆፍጠን ብላ።
<ፉዓድ ማለት?>
<ፉዓድ የወንድምሽ ጓደኛ!>
<ወንድሜ ነዋ!> ለማስቀየስ ሞከረች።
<አትዋሽ!> በጣም እየተናደደች መጣች።
<ሁሉም ሰው ምንሽ ነው እያለ ይጠይቀኛል። እኔና እሱ ግን እንደ እህትና ወንድም....> አላስጨረሰቻትም።
<ክርስቲ ከዚህ በላይ ባትዋሺኝ ምን ይመስልሻል? ፋፊ ሁሉንም ነገር ነግሮኛል። ቴሌግራም ላይ ያወራናቸውን ሁላ እንደምታነቢ ጭምር..> አለቻት። ክርስቲና አለቀሰች። ምን አስለቀሳት?
<ኹሉዴ ማርያምን እኔ አልወደውም። መጀመሪያም በሱ ስልክ ፎቶ እንድንነሳ ያረኩት እኔ አንቺ ጋ እንዲሆን ስለምፈልግ ነው እንጂ እኔ አልፈልገውም... አሁንም ላስታርቃችሁ እችላለሁ!> አለቻት አሁንም እያለቀሰች። ኹሉድ ይበልጥ ተናደደች። እንዴት እንደዚህ ታስበኛለች? እኔ አሻንጉሊት ነኝ እንዴ ከፈለገችው ወንድ ጋ እንድሆን የምታደርገኝ?
<ክርስቲ! እንኳን እንደገና ልንመለስ ቀርቶ ከዚህ በፊት አብረን የነበርንባቸው ጊዜያቶች ሁላ ፀፅተውኛል። ቢችል አጠገቤ እንዳይደርስ! ምናልባትም ሙስሊም ብትሆኚ ያልኩሽ በደምብ የሚገባሽ ይመስለኛል!> ብላት ወደ ቤቷ ሄደች። ከዛች ቀን በኋላ የክርስቲና እና ኹሉድ ግንኙነት እየቀዘቀዘ መጣ። አስረኛ ክፍልን እንደምንም ከክርስቲ ጋ ከተማረች በኋላ አስራ አንደኛ ክፍልን ሌላ ትምህርት ቤት ተመዘገበች። እዛም ነው ከእኔ ጋ የተገናኘነው። ኹሉዴ ከምላችሁ በላይ ተግባቢ ናት። ምናልባትም ያለፈውን ታሪኳን ላለማስታወስ ስትልም ይሆናል በሳቋ ለመደበቅ የምትሞክረው። ከእኔ ግን መሸሸግ አልቻለችም ነበር። አሁንም ታሪኳን ስታገባድድልኝ ወደ ቤት እየተመለስን ባለበት ሰዓት ነበር። አላህዬ ሲለው ደግሞ ሁለቱም ፉዓዶች ከፊት ለፊታችን ወደ እኛ ሲመጡ ተመለከትናቸው። ኹሉድ ፈጠን አለችና <ሪናዬ በአላህ ዝም ብለሽ አውሪኝ ባላየ እንዳልፍ> አለችኝ። የኔ ነገር! ወሬው ከዬት ይምጣልኝ? ለወትሮውማ ከኹሉድ ጋ የምናወራው ብናጣ የምንተርበው አናጣም ነበር። የዛኔ ግን ጠፋብኝ። እኛም እየሄድን እነሱም እየመጡ አጠገባችን ሲደርሱ ኹሉድ ሳቋን ለቀቀችው። ተናደድኩ የምር! እነሱም ስትስቅ ገባቸው መሰል <አሰላሙ አለይኩም> ብለውን አለፉ። ኹሉድ <ወአለይኩም ሰላም> ካለች በኋላ በራሷ ተናዳ በእጇ የያዘችውን ባይንደር መደብደብ ጀመረች።
<አንቺ እኮ ችግር አለብሽ! ለምን ሳቅሽ?> አልኳት እየተናደድኩ።
<ባክሽ ልክ ፉዲን ሳየው መጀመሪያ ላይ ለሰባህ "እኔ እንደዚህ አይነት ነገር አይመቸኝም" ሊል የደወለው ስልክ ትዝ አለኝ። አላስቻለኝማ!> አለችኝ። አሁንም እየሳቀች። እኔም ፈገግ አልኩ።
<ግን ፉዲ አሁንም.....> አልኳት።
<አዎን! አሁንም.. ሰባህን ይጠብቃታል። አሁንም ይወዳታል!> አለችኝ። ገረመኝ! እንዲህ በቃላት የተጀመረ ፍቅር እዚህ ይደርሳል ብሎ የገመተ ማን ነበር?
ቆይ ግን ፍቅር ምንድን ነው? በስድስት ፊደላት ብቻ ልብን ሰርስሮ ገብቶ ህይወትን የሚያቃውስ መሳሪያ ልበለው? ወይስ ላይ ላዩን ብቻ የሚነገር፤ በፊልም እና ልብ ወለዶች ብቻ ደምቆ የሚታይ ወሸት የሆነ ዓለም ልበለው? ትርጉሙ እስካሁን ሊገባኝ አልቻለም! እንዲገባኝም አልፈቀድኩለትም! ጊዜ ማባከን ስለ
628 views17:54